የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘመናዊቷ የኤዶም አምሳያ ተጠርጋ ትጠፋለች
    “የሰላሙ መስፍን“ ሲገዛ በምድር ዙሪያ የሚገኝ ዋስትና ያለው ሕይወት
    • 11, 12. በኢሳይያስ 34:10–15 ላይ በተሰጠው ትንቢታዊ መግለጫ መሠረት የኤዶም ምድር ምን ይሆናል? እንደዚህ ያለው የምድሪቱ ሁኔታስ እስከ ምን ያህል ጊዜ ይቀጥላል?

      11 የኢሳይያስ ትንቢት እንዲህ በማለት ይቀጥላል:- “ከትውልድ እስከ ትውልድም ድረስ ባድማ ሆና ትኖራለች፣ ለዘላለም ዓለም ማንም አያልፍባትም። ጭልፊትና ጃርት ግን ይወርሷታል፤ ጉጉትና ቁራም ይኖሩባታል፤ በላይዋም የመፍረስ ገመድ የባዶነት ቱንቢ ይዘረጋባታል። መሳፍንቶቿን ወደ መንግሥት ይጠራሉ፣ ነገር ግን ማንም አይገኝባትም አለቆችዋም ሁሉ ምናምኖች ይሆናሉ። በአዳራሽዋም እሾህ በቅጥሮቿም ሳማና አሜኬላ ይበቅሉባታል፤ የቀበሮም ማደሪያና የሰጎን ስፍራ ትሆናለች። የምድረበዳም አራዊት ከተኩሎች ጋር ይገናኛሉ፣ አጋንንትም እርስ በርሳቸው ይጠራራሉ፤ ጅንም በዚያ ትኖራለች ለእርስዋም ማረፊያ ታገኛለች። በዚያም ዋሊያ ቤትዋን ትሠራለች እንቁላልም ትጥላለች”— ኢሳይያስ 34:10–15

      12 በሰዎች በኩል ኤዶም “የባዶነት” ምድር ትሆናለች። የምድረበዳም አራዊት፣ ወፎችና እባቦች ብቻ የሚኖሩባት ጠፍ መሬት ትሆናለች። ይህ የምድሪቱ ደርቆ የመሰነጣጠቅ ሁኔታ ቁጥር 10 ላይ እንደተገለጸው “ለዘላለም ዓለም” መቀጠል ነበረበት። ለቀድሞ ነዋሪዎችዋ ምንም እንደገና የመመለስ ተስፋ አልነበራቸውም።— አብድዩ 18

      13. “በይሖዋ መጽሐፍ” ውስጥ ስለ ሕዝበ ክርስትና ምን ተተንብዮአል? ይህስ መጽሐፍ ምንድን ነው?

      13 ይህ በዘመናዊቷ የኤዶም አምሳያ በሕዝበ ክርስትና ላይ ለሚመጣው ከባድ መከራ እንዴት ያለ ጥላ ነው! እርስዋ ምስክሮቹን በጭካኔ የምታሳድደው የይሖዋ አምላክ ክፉ ጠላት እንደሆነች አሳይታለች። ስለዚህ ከአርማጌዶን በፊት የሚፈጸመው እየቀረበ ያለው ጥፋትዋ “[በይሖዋ (አዓት)] መጽሐፍ” ተተንብዮአል። (ኢሳይያስ 34:16) ይህ “የይሖዋ መጽሐፍ” ልዩ በሆነ መንገድ ጠላቶቹ ከሆኑትና ሕዝቡን ከሚጨቁኑት ጋር ሒሳብ በዝርዝር የሚተሳሰብበት መጽሐፍ ነው። ‘በይሖዋ መጽሐፍ’ ውስጥ ስለ ጥንትዋ ኤዶም የተነገረው ሁሉ እውነት ሆኗል፤ ይህም በዘመናዊቷ ኤዶም በሕዝበ ክርስትና ላይ ትንቢቱ በተመሳሳይ እውነት እንደሚሆን ዋስትና ይሰጣል።

  • ዘመናዊቷ የኤዶም አምሳያ ተጠርጋ ትጠፋለች
    “የሰላሙ መስፍን“ ሲገዛ በምድር ዙሪያ የሚገኝ ዋስትና ያለው ሕይወት
    • 15, 16. በራእይ 17 እና 18 እንዲሁም በኢሳይያስ 34 ላይ እንደ ተተነበየው የሕዝበ ክርስትና የወደፊት ሁኔታ ምንድን ነው?

      15 የሕዝበ ክርስትና የወደፊት ሁኔታ በእርግጥም የጨለመ ነው። ፖለቲካዊ ወዳጆቿን ለማባበልና እርስዋን ፈጽሞ ለማጥፋት የጥቃት ርምጃ ለመውሰድ በአንድነት እንዳይሰበሰቡ ለማድረግ የምትችለውን ሁሉ በማድረግ ላይ ነች፣ ይሁን እንጂ በከንቱ ነው!

      16 በራእይ ምዕራፍ 17 እና 18 መሠረት ሁሉን የሚችለው አምላክ ይሖዋ በታላቂቱ ባቢሎን ይኸውም በሁሉም አካሎቿና በሕዝበ ክርስትናም ላይ ጭምር አውሬያዊ እርምጃ ለመውሰድ ፖለቲካዊውንና ወታደራዊ ኃይላቸውን እንዲሰጡ በልባቸው ያደርጋል። ይህም ከመላዋ ምድር የሐሰት ክርስትናን ያስወግዳል። የሕዝበ ክርስትና ሁኔታ በኢሳይያስ 34 ላይ ከተለገጸው የጨለመ ሁኔታ ጋር የሚመሳሰል ይሆናል። ታላቂቱ ባቢሎንን በሚያጠፉት ብሔራት ላይ የሚመጣውን ወሳኙን ‘ሁሉን በሚችለው አምላክ ታላቅ ቀን የሚሆነውን ጦርነት’ ለማየት በሕይወት አትቆይም። የኤዶም አምሳያ የሆነችው ሕዝበ ክርስትና ከምድር ገጽ ላይ “ለዓለምና ለዘላለም” ሙሉ በሙሉ ትጠፋለች።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ