የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ከተስፋይቱ ምድር የሚገኙ ጠቃሚ ትምህርቶች
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | ነሐሴ 15
    • የቀርሜሎስ ኮረብታ

      በእንግሊዝኛ ካርሜል የሚለው ስም ትርጉም “ፍሬያማ” ማለት ነው። በሰሜን በኩል 50 ኪሎ ሜትር ያህል ርዝመት ያለው ለም መሬት በወይን ተክል፣ በወይራ እርሻና በፍራፍሬ ዛፎች የተሸፈነ ነው። የዚህ ኮረብታማ ሸንተረር ግርማና ውበት የማይረሳ ነው። ኢሳይያስ 35:2 እንደገና የተቋቋመው የእስራኤል ምድር ምርታማ በመሆኑ ምክንያት ያገኘውን ክብር ለማመልከት ‘የቀርሜሎስ ግርማ’ በማለት ይገልጸዋል።

  • ከተስፋይቱ ምድር የሚገኙ ጠቃሚ ትምህርቶች
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | ነሐሴ 15
    • የቀርሜሎስ ሸንተረር አሁንም በፍራፍሬዎች፣ በወይራ ዛፎችና በወይን ተክሎች የተሸፈነ ነው። በጸደይ ወራት እነዚህ ሸንተረሮች በሚያማምሩ አበቦች ይሸፈናሉ። ሰሎሞን የሚያምረውን ጠጉሯን ወይም ውብ የሆነውን የራሷን ቅርጽ ለመግለጽ “የራስሽ ቅርጽ እንደ ቀርሜሎስ ተራራ ነው” በማለት ሱላማጢሷን ሴት በማድነቅ ሰሎሞን ተናግሯል።—መኃልየ መኃልይ 7:5 የ1980 ትርጉም

      ኮረብታማው ቀርሜሎስ የተላበሰው ውበት ይሖዋ በዘመናዊ የአምልኮ ድርጅቱ ላይ አትረፍርፎ ያፈሰሰውን መንፈሳዊ ውበት እንድናስታውስ ያደርገናል። (ኢሳይያስ 35:1, 2) በእርግጥም የይሖዋ ምሥክሮች በመንፈሳዊ ገነት ውስጥ ይኖራሉ። ንጉሥ ዳዊት “ለእኔ የለገሥኸው ስጦታ እንዴት ድንቅ ነው! እጅግም መልካም ነው” በማለት ከገለጸው አባባል ጋር ይስማማሉ።—መዝሙር 16:6 የ1980 ትርጉም

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ