-
ይሖዋ በሐሰተኛ አስተማሪዎች ላይ ያስተላለፈው ፍርድመጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 1
-
-
17. (ሀ) ኤርምያስ በክፉዋ ኢየሩሳሌም ላይ ምን ይመጣባታል ብሎ ተናግሮ ነበር? (ለ) በቅርቡ ሕዝበ ክርስትና ምን ይደርስባታል?
17 የሕዝበ ክርስትና የሐሰት አስተማሪዎች ከታላቁ ፈራጅ ከይሖዋ ምን ዓይነት ፍርድ ይቀበላሉ? ቁጥር 19, 20, 39 እና 40 መልሱን ይሰጠናል፦ “እነሆ፣ የእግዚአብሔር ዐውሎ ነፋስ፣ እርሱም ቁጣው፣ የሚያገለባብጥ ዐውሎ ነፋስ ወጥቶአል፤ የዓመፀኞችን ራስ ይገለባብጣል። የእግዚአብሔር ቁጣ የልቡን አሳብ ሠርቶ እስኪፈጽም ድረስ አይመለስም፤ . . . እነሆ፣ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ። የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።” ይህ ሁሉ በክፉዋ ኢየሩሳሌምና በቤተ መቅደሷ ላይ በትክክል ተፈጽሟል። አሁን ደግሞ ክፉዋ ሕዝበ ክርስትና መዓት ይመጣባታል!
-
-
ይሖዋ በሐሰተኛ አስተማሪዎች ላይ ያስተላለፈው ፍርድመጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 1
-
-
21. (ሀ) ኢየሩሳሌም በ607 ከዘአበ የጠፋችው ለምን ነበር? (ለ) ከኢየሩሳሌም ጥፋት በኋላ በሐሰተኞቹ ነቢያት ላይ ምን ደረሰ? በእውነተኞቹ የይሖዋ ነቢያትስ ላይ? ይህስ በዛሬው ጊዜ ለኛ ምን ማስተማመኛ ይሰጠናል?
21 የይሖዋ ፍርድ በኤርምያስ ዘመን የተፈጸመው ባቢሎናውያን ኢየሩሳሌምን በ607 ከዘአበ ባጠፉ ጊዜ ነበር። በትንቢት እንደተነገረው በዚያ ጊዜ የደረሰው ጥፋት አንገተ ደንዳናና ከሃዲ የነበሩትን እስራኤላውያን ‘የሚያዋርድና’ ‘የሚያሳፍር’ ነበር። (ኤርምያስ 23:39, 40 የ1980 ትርጉም) በተደጋጋሚ ያቃለሉት ይሖዋ የክፋታቸውን ውጤት እንዲያጭዱ ፈጽሞ የጣላቸው መሆኑን አረጋግጧል። በመጨረሻው የእብሪተኞቹ ሐሰተኛ ነቢያት አፍ ተዘጋ። የኤርምያስ አፍ ግን ትንቢትን መናገሩን አላቋረጠም። ይሖዋ አልጣለውም። በዚህ ትንቢታዊ ጥላ መሠረት ይሖዋ ከባድ የሆነው የፍርዱ ውሳኔ የሕዝበ ክርስትናን ቀሳውስትና የቀሳውስቱን ውሸት ያመኑትን ሰዎች አድቅቆ ሕይወት አልባ ሲያደርግ የኤርምያስን ክፍል ግን አይጥልም።
-