-
ይሖዋን “የሚያውቅ ልብ” አለህ?መጠበቂያ ግንብ—2013 | መጋቢት 15
-
-
8, 9. አብዛኞቹ አይሁዳውያን ከልባቸው ጋር በተያያዘ ምን ማድረግ አስፈልጓቸው ነበር?
8 አምላክ አይሁዳውያን ሊያደርጉት የሚገባውን ነገር በተመለከተ የሰጣቸው ማሳሰቢያ ‘ያልተገረዘ ልብ’ የሚለው አነጋገር ምን ማለት እንደሆነ ፍንጭ ይሰጠናል፦ “እናንተ የይሁዳ ሰዎች፣ የኢየሩሳሌምም ነዋሪዎች . . . የልባችሁንም ሸለፈት አስወግዱ፤ አለዚያ ስለ ሠራችሁት ክፋት፣ ቍጣዬ እንደ እሳት ይንበለበላል።” ይሁንና የሠሩት ክፋት ከየት የመነጨ ነበር? ከውስጥ ይኸውም ከልባቸው የመነጨ ነበር። (ማርቆስ 7:20-23ን አንብብ።) አዎ፣ አምላክ በኤርምያስ አማካኝነት አይሁዳውያኑ መጥፎ ነገር እንዲሠሩ ያነሳሳቸው ምን እንደሆነ በትክክል መርምሮ ደርሶበታል። ልባቸው እልኸኛና ዓመፀኛ ነበር። ውስጣዊ ፍላጎታቸውና አስተሳሰባቸው እሱን አላስደሰተውም። (ኤርምያስ 5:23, 24፤ 7:24-26ን አንብብ።) አምላክ “ለእግዚአብሔር ተገረዙ፤ የልባችሁንም ሸለፈት አስወግዱ” ብሏቸዋል።—ኤር. 4:4፤ 18:11, 12
9 በመሆኑም በሙሴ ጊዜ እንደነበሩት እስራኤላውያን ሁሉ በኤርምያስ ዘመን የነበሩት አይሁዳውያንም ምሳሌያዊ የልብ ቀዶ ሕክምና ማድረግ ይኸውም ‘ልባቸውን መገረዝ’ አስፈልጓቸው ነበር። (ዘዳ. 10:16፤ 30:6) ‘የልባቸውን ሸለፈት መግረዝ’ ሲባል ልባቸው ደንዳና እንዲሆን ያደረገውን ነገር ይኸውም ከአምላክ ፈቃድ ጋር የሚቃረነውን አስተሳሰባቸውን፣ ፍላጎታቸውን ወይም ዝንባሌያቸውን ማስወገድ ማለት ነው።—ሥራ 7:51
-
-
ይሖዋን “የሚያውቅ ልብ” አለህ?መጠበቂያ ግንብ—2013 | መጋቢት 15
-
-
11, 12. (ሀ) እያንዳንዳችን ልባችንን መመርመር ያለብን ለምንድን ነው? (ለ) አምላክ ምን ያደርጋል ብለን መጠበቅ አይኖርብንም?
11 ይሖዋ እያንዳንዳችን በእሱ ፊት ተቀባይነት ያለው አቋም እንድንይዝና ይህን አቋሟችንን ጠብቀን እንድንኖር ይፈልጋል። ኤርምያስ ጻድቁን ሰው በተመለከተ ሲናገር “ጻድቁን የምትፈትን ልብንና አእምሮን የምትመረምር፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሆይ” ብሏል። (ኤር. 20:12) ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ የጻድቁን ሰው ልብ እንኳ የሚመረምር ከሆነ እኛም ልባችንን በሐቀኝነት መመርመር አይኖርብንም? (መዝሙር 11:5ን አንብብ።) እንዲህ በምናደርግበት ጊዜ በቸልታ ልናልፈው የማይገባ አመለካከት ወይም ግብ እንዳለን አሊያም ደግሞ አንድ ዓይነት ስሜት እንደተጠናወተን እንገነዘብ ይሆናል። ልባችን በተወሰነ መጠን እንዲደነዝዝ ያደረገ ምሳሌያዊ ‘የልብ ሸለፈት’ እንዳለ ልናስተውልና ማስወገድ እንደሚኖርብን ልንገነዘብ እንችላለን። በዚህ መንገድ ምሳሌያዊ የልብ ቀዶ ሕክምና እናደርጋለን። ምሳሌያዊ ልብህን መመርመርህ ጥሩ እንደሆነ ከተገነዘብክ ትኩረት ማድረግ የሚያስፈልግህ ምን ላይ ነው? አስፈላጊውን ማስተካከያ ማድረግ የምትችለውስ እንዴት ነው?—ኤር. 4:4
-