የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ይሖዋን በመፍራት ደስታ ማግኘትን መማር
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | መጋቢት 15
    • 14, 15. (ሀ) ይሖዋ እስራኤላውያን ከባቢሎን ምርኮ ነጻ ወጥተው ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው እንደሚመለሱ አስቀድሞ ሲናገር ለሕዝቡ ምን እንደሚሰጣቸው ቃል ገብቶ ነበር? (ለ) ይሖዋ በሕዝቡ ልብ ውስጥ ፈሪሃ አምላክን ለመትከል ምን አድርጓል? (ሐ) እስራኤላውያን ከይሖዋ መንገዶች ዘወር ያሉት ለምንድን ነው?

      14 ይሖዋ ለሕዝቦቹ ይህን የመሰለ አምላክን የሚፈራ ልብ እንደሚሰጥ ቃል ገብቷል። በኤርምያስ 32:37–39 ላይ እንደምናነበው ስለ እስራኤል መታደስ አስቀድሞ ከተናገረ በኋላ እንዲህ አለ፦ “ወደዚህም ስፍራ እመልሳቸዋለሁ፣ ተዘልለውም እንዲኖሩ አደርጋለሁ፤ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ። ለእነርሱም ከእነርሱም በኋላ ለልጆቻቸውም መልካም ይሆንላቸው ዘንድ ለዘላለም እንዲፈሩኝ አንድ ልብና አንድ መንገድ እሰጣቸዋለሁ።” በቁጥር 40 ላይ ደግሞ “ከእኔም ዘንድ ፈቀቅ እንዳይሉ መፈራቴን በልባቸው ውስጥ አኖራለሁ” በማለት አምላክ የገባላቸውን የተስፋ ቃል አጠናክሮታል። ይሖዋ በዚህ የተስፋ ቃሉ መሠረት በ537 ከዘአበ ፈሪሃ አምላክ የነበራቸውን አይሁዳውያን ቀሪዎች ወደ ኢየሩሳሌም መልሷል። ይሁን እንጂ ‘ዘወትር እንዲፈሩኝ አንድ ልብና አንድ መንገድ እሰጣቸዋለሁ’ በማለት የሰጣቸው የተቀረው የዚህ የተስፋ ቃልስ? የጥንቱ የእስራኤል ብሔር ከባቢሎን ከተመለሰ በኋላ ከይሖዋ ዘወር ያለውና በዚህም ምክንያት ቤተ መቅደሱ በ70 እዘአ ዳግመኛ ላይሠራ ለዘላለም የጠፋው ለምንድን ነው?

  • ይሖዋን በመፍራት ደስታ ማግኘትን መማር
    መጠበቂያ ግንብ—1995 | መጋቢት 15
    • 16. ይሖዋ አምላካዊ ፍርሃትን በእነማን ልብ ውስጥ ተክሏል?

      16 ሆኖም አምላክ በሕዝቦቹ ልብ ውስጥ አምላክን መፍራትን ለመትከል የገባው የተስፋ ቃል ከንቱ ሆኖ አልቀረም። ሰማያዊ ተስፋ ከተሰጣቸው ክርስቲያኖች፣ ማለትም ከመንፈሳዊ እስራኤል ጋር አዲስ ቃል ኪዳን ገብቷል። (ኤርምያስ 31:33፤ ገላትያ 6:16) አምላክ እነዚህን መንፈሳዊ እስራኤላውያን በ1919 የዓለም የሐሰት ሃይማኖት ግዛት ከሆነችው ከታላቂቱ ባቢሎን ግዞት ነፃ አወጣቸው። እርሱን የመፍራት ባሕርይም በልባቸው ውስጥ ጠልቆ እንዲተከል አድርጓል። ይህም ለእነርሱም ሆነ የመንግሥቲቱ ምድራዊ ተገዥዎች በመሆን ሕይወት የማግኘት ተስፋ ላላቸው “እጅግ ብዙ ሰዎች” ብዙ ጥቅሞች አስገኝቷል። (ኤርምያስ 32:39፤ ራእይ 7:9) ይሖዋን መፍራት በእነዚህ እጅግ ብዙ ሰዎች ልብ ውስጥም ተተክሏል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ