የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ይሖዋ ሰላምንና እውነትን አትረፍርፎ ይሰጣል
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥር 1
    • “እፈውሳቸውማለሁ፤ የሰላምንና የእውነትን ብዛት እገልጥላቸዋለሁ።”—ኤርምያስ 33:6

  • ይሖዋ ሰላምንና እውነትን አትረፍርፎ ይሰጣል
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥር 1
    • 3. ይሖዋ በኤርምያስ በኩል የተናገራቸው ቃላት ሲፈጸሙ እስራኤል ስለ ሰላም ለሁለተኛ ጊዜ አስፈላጊ የሆነ ትምህርት እንድታገኝ ያደረጓት ታሪካዊ ክንውኖች የትኞቹ ናቸው?

      3 ይሁን እንጂ ይሖዋ ኢየሩሳሌም ከመጥፋቷ በፊት ለእስራኤል ሰላም የሚያመጣው እሱ እንጂ ግብፅ እንዳልሆነች ገልጾ ነበር። በኤርምያስ በኩል የሚከተለውን ተስፋ ሰጥቷቸው ነበር፦ “እፈውሳቸውማለሁ፤ የሰላምንና የእውነትን ብዛት እገልጥላቸዋለሁ። የይሁዳን ምርኮና የእስራኤልን ምርኮ እመልሳለሁ፣ ቀድሞም እንደ ነበሩ አድርጌ እሠራቸዋለሁ።” (ኤርምያስ 33:6, 7) በ539 ከዘአበ ባቢሎን ድል ስትደረግና እስራኤላውያን ምርኮኞች ነፃ እንዲወጡ ጥሪ ሲቀርብ ይሖዋ የሰጠው ተስፋ መፈጸም ጀመረ። (2 ዜና መዋዕል 36:22, 23) በ537 ከዘአበ መገባደጃ ላይ አንድ የእስራኤላውያን ቡድን ከ70 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በእስራኤል ምድር የዳስ በዓልን አከበረ! ከበዓሉ በኋላ የይሖዋን ቤተ መቅደስ መሥራት ጀመሩ። ይህ ሁኔታ ምን ስሜት አሳድሮባቸው ነበር? የታሪክ መዝገቡ “የእግዚአብሔርም ቤት ስለ ተመሠረተ ሕዝቡ ሁሉ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ በታላቅ ድምፅ እልል አሉ” ይላል።—ዕዝራ 3:11

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ