-
የአርኪኦሎጂ ግኝቶች መጽሐፍ ቅዱስን ይደግፋሉ?ንቁ!—2007 | ኅዳር
-
-
በ2005 አርኪኦሎጂስቶች የንጉሥ ዳዊትን ቤተ መንግሥት እናገኛለን ብለው ባሰቡበት ቦታ ላይ ሲቆፍሩ ከ2,600 ዓመታት በፊት የአምላክ ነቢይ በነበረው በኤርምያስ ዘመን ባቢሎናውያን ኢየሩሳሌምን ድምጥማጧን ባጠፉበት ወቅት እንደፈራረሰ ያመኑበትን የሕንፃ ፍርስራሽ አገኙ። ሕንፃው የዳዊት ቤተ መንግሥት ይሁን አይሁን በውል አልታወቀም። ይሁን እንጂ ኤላት ማሳር የተባሉ አንዲት አርኪኦሎጂስት ከፍርስራሹ ውስጥ “የሾቪ ልጅ፣ የሸሌምያሁ ልጅ የየሁካል ንብረት” የሚል 1 ሴንቲ ሜትር ስፋት ያለው የሸክላ ማኅተም [5] አገኙ። በግልጽ ለማየት እንደሚቻለው በሸክላው ላይ ያረፈው ማኅተም በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኤርምያስን እንደተቃወመ የተነገረለት የሁካል (ጀሁካል ወይም ዮካል) የተባለ አንድ አይሁዳዊ ባለ ሥልጣን ማኅተም ነበር።—ኤርምያስ 37:3፤ 38:1-6
የሁካል በዳዊት ከተማ ውስጥ በአንድ የሸክላ ማኅተም ላይ ስሙ ከተገኘው ከሳፋን ልጅ ከገማርያ ቀጥሎ “በሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝ የቤተ መንግሥት ባለ ሥልጣን” እንደነበረ ማሳር ተናግረዋል። መጽሐፍ ቅዱስ የሸሌምያ (ሸሌምያሁ) ልጅ የሁካል የይሁዳ መስፍን እንደነበረ ይጠቁማል። ይህ ማኅተም ከመገኘቱ በፊት ዮካል መጽሐፍ ቅዱስ ከሚናገረው ውጭ በእርግጥ በሕይወት የነበረ ሰው መሆኑን የሚያሳይ ማስረጃ አልነበረም።
-
-
የአርኪኦሎጂ ግኝቶች መጽሐፍ ቅዱስን ይደግፋሉ?ንቁ!—2007 | ኅዳር
-
-
3: Musée du Louvre, Paris; 4: Photograph taken by courtesy of the British Museum; 5: Gabi Laron/Institute of Archaeology/Hebrew University © Eilat Mazar
-