-
“አንድ እረኛ . . . አስነሳለሁ”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
5. እንቆቅልሹ ምንድን ነው?
5 ሕዝቅኤል 17:3-10ን አንብብ። እንቆቅልሹ የሚከተለው ነው፦ አንድ “ታላቅ ንስር” በአንድ አርዘ ሊባኖስ ‘አናት ላይ ያለውን ቀንበጥ’ ቀጥፎ ‘በነጋዴዎች ከተማ ተከለው።’ ከዚያም ንስሩ “ከምድሪቱ ዘር የተወሰነውን ወስዶ” “ብዙ ውኃ ባለበት” ለም የሆነ መሬት ላይ ዘራው። ዘሩ በቀለና አድጎ ‘የተንሰራፋ የወይን ተክል’ ሆነ። ቀጥሎ ደግሞ ሌላ “ታላቅ ንስር” ብቅ አለ። የወይን ተክሉም ብዙ ውኃ ባለበት ሌላ መሬት ላይ መተከል ስለፈለገ “በታላቅ ጉጉት” ሥሮቹን ወደ ሁለተኛው ንስር ዘረጋ። ይሖዋ ሥሮቹ ተነቅለው እንደሚጣሉና ‘ሙሉ በሙሉ እንደሚደርቁ’ በመግለጽ የወይን ተክሉን ድርጊት አወገዘ።
የመጀመሪያው ታላቅ ንስር የባቢሎንን ንጉሥ ናቡከደነጾርን ያመለክታል (አንቀጽ 6ን ተመልከት)
6. የእንቆቅልሹን ፍቺ ተናገር።
6 የእንቆቅልሹ ፍቺ ምንድን ነው? (ሕዝቅኤል 17:11-15ን አንብብ።) በ617 ዓ.ዓ. የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነጾር (የመጀመሪያው “ታላቅ ንስር”) ኢየሩሳሌምን ከበበ። ከዚያም የይሁዳ ንጉሥ የነበረውን ንጉሥ ዮአኪንን (‘አናት ላይ ያለውን ቀንበጥ’) ከዙፋኑ አንስቶ ወደ ባቢሎን (‘የነጋዴዎች ከተማ’) ወሰደው። ናቡከደነጾር ሴዴቅያስን (ከምድሪቱ ንጉሣዊ ዘር አንዱን) ወስዶ በኢየሩሳሌም በሚገኘው ዙፋን ላይ አስቀመጠው። አዲሱ የይሁዳ ንጉሥ ታማኝ ገባር ንጉሥ ለመሆን በአምላክ ስም እንዲምል ተደርጎ ነበር። (2 ዜና 36:13) ሴዴቅያስ ግን መሐላውን ንቆ በባቢሎን ንጉሥ ላይ በማመፅ የግብፁ ንጉሥ ፈርዖን (ሁለተኛው “ታላቅ ንስር”) ወታደራዊ እርዳታ እንዲሰጠው ጠየቀ፤ ሆኖም ያሰበው አልተሳካለትም። ይሖዋ ሴዴቅያስ መሐላውን በማፍረስ የፈጸመውን ክህደት አውግዟል። (ሕዝ. 17:16-21) በመጨረሻም ሴዴቅያስ ከዙፋኑ እንዲወርድ የተደረገ ሲሆን በባቢሎን እስር ቤት ውስጥ እያለ ሞተ።—ኤር. 52:6-11
-
-
ስለ መሲሑ የሚናገር ትንቢት—የሚያምር የአርዘ ሊባኖስ ዛፍየይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
3. ሴዴቅያስ በይሖዋ ላይ በማመፅ ወታደራዊ እርዳታ ለማግኘት ግብፅን ጠየቀ
-