-
ስለ መሲሑ የሚናገር ትንቢት—የሚያምር የአርዘ ሊባኖስ ዛፍየይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
4. ይሖዋ ልጁን በሰማያዊቷ የጽዮን ተራራ ላይ ተከለው
-
-
“አንድ እረኛ . . . አስነሳለሁ”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
9 ትንቢቱ ምን ይላል? (ሕዝቅኤል 17:22-24ን አንብብ።) አሁን እርምጃ የሚወስዱት ታላላቆቹ ንስሮች ሳይሆኑ ይሖዋ ራሱ ነው። ይሖዋ “ከረጅሙ አርዘ ሊባኖስ ጫፍ ላይ” ቀንበጥ ቀጥፎ “ረጅምና ግዙፍ በሆነ ተራራ ላይ” ይተክለዋል። ይህ ቀንበጥ አድጎ በመንሰራፋት “የሚያምር አርዘ ሊባኖስ ይሆናል። በሥሩም የወፍ ዓይነቶች ሁሉ ይኖራሉ።” በዚያ ጊዜ “የዱር ዛፎች ሁሉ” ይህ የሚያምር ዛፍ እንዲንሰራፋ ያደረገው ይሖዋ ራሱ እንደሆነ ያውቃሉ።
10 ትንቢቱ ፍጻሜውን ያገኘው እንዴት ነው? ይሖዋ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን ከዳዊት ንጉሣዊ ዘር (‘ከረጅሙ አርዘ ሊባኖስ’) ላይ ቀጥፎ በሰማያዊቷ የጽዮን ተራራ (‘ረጅምና ግዙፍ በሆነው ተራራ’) ላይ ተከለው። (መዝ. 2:6፤ ኤር. 23:5፤ ራእይ 14:1) በዚህ መንገድ ይሖዋ፣ በጠላቶቹ ዘንድ “ከሰዎች ሁሉ የተናቀ” ተደርጎ የተቆጠረውን ልጁን “የአባቱን የዳዊትን ዙፋን” በመስጠት ከፍ ከፍ አድርጎታል። (ዳን. 4:17፤ ሉቃስ 1:32, 33) መሲሐዊው ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ታላቅ አርዘ ሊባኖስ በመላው ምድር ላይ በመንሰራፋት ለተገዢዎቹ በሙሉ የበረከት ምንጭ ይሆንላቸዋል። በእርግጥም ልንተማመንበት የሚገባው ገዢ እሱ ነው። በኢየሱስ ንጉሣዊ አገዛዝ ጥላ ሥር በመላው ምድር የሚኖሩ ታዛዥ የሰው ልጆች “መከራ ይደርስብኛል የሚል ስጋት” ሳያድርባቸው ‘ተረጋግተው ይኖራሉ።’—ምሳሌ 1:33
-