የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “አንድ ልብ እሰጣቸዋለሁ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • 36, 37. ወደፊት በገነት ውስጥ የትኞቹ ተስፋዎች ይፈጸማሉ?

      36 ከታላቁ የአርማጌዶን ጦርነት በኋላ ኢየሱስ ግዑዟ ምድርም እንድትታደስ ያደርጋል። ኢየሱስ በሺህ ዓመት ግዛቱ ወቅት በይሖዋ የመጀመሪያ ዓላማ መሠረት የሰው ልጆች መላዋን ምድር ወደ ገነትነት እንዲለውጡ ያደርጋል። (ሉቃስ 23:43) ያን ጊዜ የሰው ልጆች እርስ በርሳቸውም ሆነ መኖሪያቸው ከሆነችው ምድር ጋር ሙሉ በሙሉ ተስማምተው ይኖራሉ። የትም ቦታ አደጋም ሆነ የሚያስፈራ ነገር አይኖርም። የሚከተለው ተስፋ ቃል በቃል ፍጻሜውን ሲያገኝ ምን ዓይነት ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል ለማሰብ ሞክር፦ “ከእነሱም ጋር የሰላም ቃል ኪዳን እገባለሁ፤ አደገኛ የሆኑ የዱር አራዊትንም ከምድሪቱ ላይ አጠፋለሁ፤ በመሆኑም በምድረ በዳ ያለስጋት ይኖራሉ፤ በጫካዎችም ውስጥ ይተኛሉ።”—ሕዝ. 34:25

      37 እስቲ የሚከተለውን በዓይነ ሕሊናህ ለመሣል ሞክር! በዚህች ሰፊ ምድር ላይ የሚገኝን የትኛውንም ቦታ ያለምንም ስጋት መጎብኘት ትችላለህ። ጉዳት ሊያደርስብህ የሚችል አንድም እንስሳ አይኖርም። ሰላምህን የሚያውክ አንዳች ነገር አይኖርም። ጥቅጥቅ ባለ ደን ውስጥ ብቻህን እየተዘዋወርክ ታላቅ ግርማ የተላበሰውን ደን ውበት ማድነቅ ትችላለህ። እንዲያውም አንዳች ጉዳት ይደርስብኝ ይሆን ብለህ ሳትሰጋ እዚያው ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወስዶህ አርፈህና ሰውነትህ ታድሶ መነሳት ትችላለህ!

      አንዲት ልጅ በምሽት ጫካ ውስጥ ዛፍ ሥር ተኝታ። ዛፉ ላይ አንድ ግስላ ተቀምጧል።

      ‘በጫካ ውስጥ’ እንኳ ያለምንም ስጋት መተኛት የሚቻልበትን ጊዜ በዓይነ ሕሊናህ ለመሣል ሞክር (አንቀጽ 36, 37⁠ን ተመልከት)

  • “አንድ ልብ እሰጣቸዋለሁ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ