የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “ሕያው ትሆናላችሁ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • “አጥንቶቹም እርስ በርስ መገጣጠም ጀመሩ”

      10. (ሀ) ሕዝቅኤል 37:7, 8 የአምላክ ሕዝቦች ምን እንደሚሆኑ ይናገራል? (ለ) ፈሪሃ አምላክ የነበራቸው ግዞተኞች እምነታቸው ቀስ በቀስ እንዲያንሰራራ የረዳቸው ምን ሊሆን ይችላል?

      10 በጥንት ጊዜ ይሖዋ ሕዝቦቹ ደረጃ በደረጃ ተመልሰው ሕያው እንደሚሆኑ ተንብዮ ነበር። (ሕዝ. 37:7, 8) ታዲያ ፈሪሃ አምላክ የነበራቸው ግዞተኞች፣ ወደ እስራኤል እንደሚመለሱ የተሰጣቸው ተስፋ እንደሚፈጸም ያላቸው እምነት ቀስ በቀስ እንዲያንሰራራ ያደረጉት ነገሮች የትኞቹ ናቸው? ተስፋቸው እንዲያንሰራራ ካደረጉት ነገሮች መካከል አንዱ ቀደም ሲል የነበሩ ነቢያት የተናገሩት ትንቢት መሆን አለበት። ለምሳሌ ኢሳይያስ “የተቀደሰ ዘር” ማለትም አይሁዳውያን ቀሪዎችን ያቀፈ ቡድን ወደ ምድሪቱ እንደሚመለስ ተንብዮ ነበር። (ኢሳ. 6:13፤ ኢዮብ 14:7-9) በተጨማሪም ሕዝቅኤል የጻፋቸው ስለ መልሶ መቋቋም የሚገልጹ በርካታ ትንቢቶች ተስፋቸውን አለምልመውላቸው እንደሚሆን አያጠራጥርም። ከዚህም ሌላ እንደ ነቢዩ ዳንኤል ያሉ ታማኝ ሰዎች በባቢሎን መኖራቸውና የባቢሎን ከተማ በ539 ዓ.ዓ. በአስደናቂ ሁኔታ መውደቋ ግዞተኞቹ ወደ አገራቸው እንደሚመለሱ የነበራቸውን ተስፋ አጠናክሮት መሆን አለበት።

  • “ሕያው ትሆናላችሁ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • 12 ከጊዜ በኋላ ደግሞ ቻርልስ ቴዝ ራስልና የሥራ ባልደረቦቹ የመጽሐፍ ቅዱስን እውነቶች ለመግለጥ በቅንዓት እንቅስቃሴ ማድረግ ሲጀምሩ አጥንቶቹ “ጅማትና ሥጋ” ለበሱ። የጽዮን መጠበቂያ ግንብ እና ሌሎች ጽሑፎች ቅን ልብ ያላቸው ሰዎች መንፈሳዊ እውነቶችን እንዲያገኙ ረድተዋል፤ በዚህ የተነሳ እነዚህ ሰዎችም ከአምላክ ቅቡዓን አገልጋዮች ጋር ተቀላቀሉ። በ1900ዎቹ ዓመታት መጀመሪያ ላይ “የፍጥረት ፎቶ ድራማ” የተባለው ፊልም፣ ያለቀለት ሚስጥር የተባለው መጽሐፍና ሌሎችም መሣሪያዎች መዘጋጀታቸው ቅቡዓን ክርስቲያኖችን ይበልጥ አጠናክሯቸዋል። ከዚያ ብዙም ሳይቆይ አምላክ ሕዝቦቹን ‘በእግራቸው እንዲቆሙ’ ለማድረግ እርምጃ ወሰደ። (ሕዝ. 37:10) ይህ የሆነው መቼና እንዴት ነው? በጥንቷ ባቢሎን የተከናወኑትን ሁኔታዎች መመልከታችን የዚህን ጥያቄ መልስ ለማግኘት ይረዳናል።

  • ንጹሕ አምልኮ ቀስ በቀስ መልሶ ተቋቋመ
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
      • ቻርልስ ቴዝ ራስልና አጋሮቹ።

        “ጅማትና ሥጋ”

        ቻርልስ ቴዝ ራስልና የሥራ ባልደረቦቹ የመጽሐፍ ቅዱስን እውነቶች ለመግለጥ እንቅስቃሴ ማድረግ ጀመሩ

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ