የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “ሕያው ትሆናላችሁ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • 9. በጥንቶቹ እስራኤላውያን ላይ በደረሰውና “በአምላክ እስራኤል” ላይ በደረሰው ነገር መካከል ምን ተመሳሳይነት አለ?

      9 የሕዝቅኤልን ትንቢቶች ጨምሮ ስለ እስራኤል መልሶ መቋቋም የሚናገሩት ትንቢቶች በወቅቱ ከነበራቸው ፍጻሜ በተጨማሪ ሌላም የላቀ ፍጻሜ አላቸው። (ሥራ 3:21) በጥንት ጊዜ የእስራኤል ብሔር ‘እንደተገደለና’ በምሳሌያዊ ሁኔታ ለበርካታ ዓመታት በድን ሆኖ እንደቆየ ሁሉ ‘የአምላክ እስራኤል’ የተባለው የቅቡዓን ክርስቲያኖች ጉባኤም በምሳሌያዊ ሁኔታ ተገድሎ ለረጅም ዓመታት ከሞት በማይተናነስ ግዞት ሥር ኖሯል። (ገላ. 6:16) የቅቡዓን ክርስቲያኖች ጉባኤ በምርኮ የቆየበት ጊዜ በጣም ረጅም ከመሆኑ የተነሳ የነበሩበት መንፈሳዊ ሁኔታ ‘በጣም ከደረቁ’ አጥንቶች ጋር የሚመሳሰል ሆኖ ነበር። (ሕዝ. 37:2) ከዚህ በፊት በነበረው ምዕራፍ ላይ እንደተብራራው የቅቡዓን ክርስቲያኖች ጉባኤ በምርኮ የተያዘው በሁለተኛው መቶ ዘመን ዓ.ም. ሲሆን ኢየሱስ ስለ ስንዴውና ስለ እንክርዳዱ የተናገረው ምሳሌ እንደሚያመለክተው ይህ ሁኔታ ለብዙ መቶ ዓመታት ዘልቋል።—ማቴ. 13:24-30

      ሕዝቅኤል በደረቁ አጥንቶች የተሞላውን ሸለቆ ሲያይ።

      ሕዝቅኤል በራእይ የተመለከታቸው ‘በጣም የደረቁ’ አጥንቶች ቅቡዓን ክርስቲያኖች ለረጅም ዘመን እንደ ሞት ባለ ግዞት ውስጥ እንደሚቆዩ ያመለክታሉ (አንቀጽ 8, 9⁠ን ተመልከት)

  • “ሕያው ትሆናላችሁ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • a ሕዝቅኤል በራእይ የተመለከታቸው አጥንቶች ‘የተገደሉ ሰዎች’ አጥንቶች እንጂ ተፈጥሯዊ በሆነ ሁኔታ የሞቱ ሰዎች አጥንቶች አልነበሩም። (ሕዝ. 37:9) በመጀመሪያ አሦራውያን አሥሩን ነገድ ያቀፈውን የእስራኤል መንግሥት፣ በኋላ ደግሞ ባቢሎናውያን ሁለቱን ነገድ ያቀፈውን የይሁዳ መንግሥት ድል ነስተው በግዞት በወሰዱበት ወቅት “መላው የእስራኤል ቤት” በምሳሌያዊ ሁኔታ ተገድሏል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ