የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “አንድ ብሔር አደርጋቸዋለሁ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • 4. ሕዝቅኤል ቀጥሎ በበትሮቹ ላይ ያደረገው ነገር ምን ያመለክታል? (በመግቢያው ላይ ያለውን ሥዕል ተመልከት።)

      4 ቀጥሎም ሕዝቅኤል “አንድ በትር ይሆኑ ዘንድ” ሁለቱን በትሮች አንድ ላይ እንዲይዛቸው ተነገረው። ግዞተኞቹ በጭንቀት ተውጠው ሕዝቅኤልን እየተመለከቱት “የእነዚህ ነገሮች ትርጉም ምን እንደሆነ አትነግረንም?” ሲሉ ጠየቁት። እሱም ትንቢታዊ ድራማው ይሖዋ ራሱ የሚያደርገውን ነገር የሚያመለክት እንደሆነ ነገራቸው። ይሖዋ ሁለቱን በትሮች በተመለከተ እንዲህ ሲል ተናግሯል፦ “አንድ በትርም አደርጋቸዋለሁ፤ እነሱም በእጄ ላይ አንድ በትር ይሆናሉ።”—ሕዝ. 37:17-19

      5. ሕዝቅኤል በድራማ መልክ ያሳየው ትንቢት ትርጉሙ ምንድን ነው? (“የሁለቱ በትሮች አንድ መሆን” የሚለውን ሣጥን ተመልከት።)

      5 ከዚያም ይሖዋ ሁለቱ በትሮች አንድ መሆናቸው ምን ትርጉም እንዳለው ገለጸ። (ሕዝቅኤል 37:21, 22⁠ን አንብብ።) ሁለቱን ነገድ ካቀፈው የይሁዳ መንግሥት የተውጣጡ ግዞተኞችና አሥሩን ነገድ ካቀፈው የእስራኤል መንግሥት (ከኤፍሬም) የተውጣጡ ግዞተኞች ወደ እስራኤል ምድር ተመልሰው በዚያ “አንድ ብሔር” ይሆናሉ።—ኤር. 30:1-3፤ 31:2-9፤ 33:7

  • የሁለቱ በትሮች አንድ መሆን
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • ሕዝቅኤል በአንድ እጁ ሁለት በትሮችን አንድ ላይ ይዞ።

      ‘በእጅህ አንድ በትር ይሆናሉ’

      በጥንት ዘመን

      በ537 ዓ.ዓ. የአምላክ ሕዝቦች ከተለያዩ ብሔራት ተመልሰው ኢየሩሳሌምን ዳግመኛ ገነቡ፤ እንዲሁም አንድ ብሔር ሆነው ይሖዋን ማምለክ ጀመሩ።

      በዘመናችን

      ከ1919 ጀምሮ የአምላክ ሕዝቦች ቀስ በቀስ ተደራጁ፤ እንዲሁም “አንድ መንጋ” ሆነው በአንድነት ይሖዋን ማገልገል ጀመሩ።

      ትንቢቱ አንድ በመሆን ላይ ያተኮረ ነው

      ትንቢቱ፣ አንድ በትር ለሁለት እንደተሰበረና በኋላ መልሶ አንድ እንደሆነ አይናገርም። ከዚህ ይልቅ ሁለት በትሮች አንድ እንደሆኑ ይገልጻል። ስለዚህ ትንቢቱ ትኩረት የሚያደርገው የእስራኤል ብሔር ተከፍሎ ሁለት መንግሥት በሆነበት መንገድ ላይ ሳይሆን ሁለቱ መንግሥታት አንድ በሆኑበት መንገድ ላይ ነው።

      ወደ ምዕራፍ 12 ከአንቀጽ 3-6, 13, 14 ተመለስ

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ