የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ሕዝቅኤል ስለ ቤተ መቅደሱ ካየው ራእይ የምናገኛቸው ትምህርቶች
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
  • “የቤተ መቅደሱ ሕግ ይህ ነው”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • በዘመናችን ከሕዝቅኤል ራእይ የምናገኘው ትምህርት

      በራእይ በታየው ቤተ መቅደስ ውስጥ መሥዋዕት ሆነው የሚቀርቡ እንስሳት።

      ሣጥን 13ሀ፦ የተለያዩ ቤተ መቅደሶች፣ የተለያዩ ትምህርቶች

      13, 14. (ሀ) ሕዝቅኤል ስለ ቤተ መቅደሱ ያየው ራእይ በእኛም ዘመን ፍጻሜውን እንደሚያገኝ እንዴት እናውቃለን? (ለ) ራእዩ በየትኞቹ ሁለት መንገዶች ይጠቅመናል? (“የተለያዩ ቤተ መቅደሶች፣ የተለያዩ ትምህርቶች” የሚለውን ሣጥን 13ሀንም ተመልከት።)

      13 ሕዝቅኤል ስለ ቤተ መቅደሱ ያየው ራእይ ለእኛስ የያዘው ትምህርት አለ? አዎ! ሕዝቅኤል በራእይ ባየው “በአንድ ትልቅ ተራራ” ላይ የሚገኝ ቤተ መቅደስና ኢሳይያስ “የይሖዋ ቤት ተራራ ከተራሮች አናት በላይ ጸንቶ [እንደሚቆም]” በተናገረው ትንቢት መካከል ተመሳሳይነት እንዳለ አስታውስ። ኢሳይያስ ትንቢቱ ፍጻሜውን የሚያገኘው “በዘመኑ መጨረሻ” ወይም “በመጨረሻዎቹ ቀኖች” እንደሆነ በግልጽ ተናግሯል። (ሕዝ. 40:2፤ ኢሳ. 2:2-4 ግርጌ፤ ሚክያስ 4:1-4⁠ንም ተመልከት።) እነዚህ ትንቢቶች ፍጻሜያቸውን የሚያገኙት በመጨረሻዎቹ ቀኖች ውስጥ ማለትም ንጹሕ አምልኮ መልሶ ከተቋቋመበትና በትልቅ ተራራ ላይ የተቀመጠ ያህል ከፍ ከፍ ከተደረገበት ከ1919 ጀምሮ ባለው ጊዜ ነው።b

      14 ስለዚህ የሕዝቅኤል ራእይ በዛሬው ጊዜ ከምናቀርበው ንጹሕ አምልኮ ጋር በተያያዘም እንደሚሠራ በእርግጠኝነት መናገር እንችላለን። ይህ ራእይ በጥንት ዘመን የነበሩትን አይሁዳውያን ግዞተኞች እንደጠቀማቸው ሁሉ እኛንም በሁለት መንገዶች ይጠቅመናል። (1) ይሖዋ ለንጹሕ አምልኮ ያወጣውን መሥፈርት እንዴት ማክበር እንደምንችል ያስተምረናል። (2) ንጹሕ አምልኮ መልሶ እንደሚቋቋምና የይሖዋን በረከት እንደምናገኝ ዋስትና ይሰጠናል።

  • ሕዝቅኤል ስለ ቤተ መቅደሱ ካየው ራእይ የምናገኛቸው ትምህርቶች
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • ሕዝቅኤል በራእይ ያየው ቤተ መቅደስ ያሉትን ዋና ዋና ገጽታዎች የሚያሳይ ሥዕል። ከገጽታዎቹ መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦ 1. ትልቅ ተራራ። 2. በዙሪያው ያለው ቅጥር። 3. በቤተ መቅደሱ ዙሪያ ያለው ሰፊ ቦታ። 4. ከቤተ መቅደሱ የሚፈሰው ወንዝ። 5. ውጨኞቹ በሮች። 6. የቤተ መቅደሱ ቅጥር። 7. ውጨኛው ግቢ። 8. በውጭ በኩል ያሉት የመመገቢያ ክፍሎች። 9. ውስጠኞቹ በሮች። 10. ውስጠኛው ግቢ። 11. መሠዊያው። 12. ቤተ መቅደሱ። አንድ ትልቅ የመንገደኞች አውሮፕላን (ርዝመቱ 75 ሜትር ገደማ ነው) ከቤተ መቅደሱ ግቢ (እያንዳንዱ ጎኑ 1555 ሜትር ነው) ጋር ሲወዳደር በጣም ትንሽ ነው።

      ንጹሕ አምልኮ ከፍ ከፍ ተደረገ፤ ጥበቃም ተደረገለት

      በራእይ የታየው ቤተ መቅደስ የሚገኘው “ትልቅ ተራራ” (1) ላይ ነው። እኛስ ንጹሕ አምልኮን በሕይወታችን ውስጥ በማስቀደም ከፍ ከፍ እንዲል እያደረግነው ነው?

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ