-
“ቤተ መቅደሱ” እና “አለቃው” በዛሬው ጊዜመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
3. ረጅም ከፍታ ካለው ጣሪያና በቤተ መቅደሱ መግቢያ ግድግዳዎች ላይ ከተቀረጹት ምስሎች ምን እንማራለን?
3 ራሳችንን ይህን ራእያዊ ቤተ መቅደስ በመጎብኘት ላይ እንዳለን አድርገን እናስብ። ሰባት ደረጃዎች ከወጣን በኋላ በጣም ግዙፍ ከሆኑት በሮች ወደ አንዱ እንሄዳለን። እዚህ በር ላይ እንደቆምን ከፊታችን በምንመለከተው ነገር ተደንቀን እንቆማለን። የጣሪያው ከፍታ ከ30 ሜትር ይበልጣል! ይህ ደግሞ ወደ ይሖዋ የአምልኮ ዝግጅት ለመግባት የሚያስፈልገው ብቃት በጣም ከፍተኛ መሆኑን ያስታውሰናል። በመስኮቶቹ በኩል የሚገባው የብርሃን ጨረር በግድግዳው ላይ የተቀረጹትን የዘንባባ ዛፎች ምስል አድምቆ ያሳየናል። የዘንባባ ዛፎች በቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ ንጽሕናን ለማመልከት ተሠርቶባቸዋል። (መዝሙር 92:12፤ ሕዝቅኤል 40:14, 16, 22) ወደዚህ ቅዱስ ሥፍራ መግባት የሚችሉት ሥነ ምግባራዊም ሆነ መንፈሳዊ ንጽሕናቸውን የሚጠብቁ ብቻ ናቸው። እኛም አምልኮታችን በይሖዋ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ንጽሕናችንን ጠብቀን መኖር እንፈልጋለን።—መዝሙር 11:7
-
-
“ቤተ መቅደሱ” እና “አለቃው” በዛሬው ጊዜመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
5. (ሀ) በሕዝቅኤል ራእይና በራእይ 7:9-15 ላይ ተመዝግቦ በሚገኘው የዮሐንስ ራእይ መካከል ምን ተመሳሳይነት አለ? (ለ) በሕዝቅኤል ራእይ ላይ በውጨኛው አደባባይ ሲያመልኩ የታዩት 12ቱ ነገዶች እነማንን ያመለክታሉ?
5 የመተላለፊያው በር ሕዝቡ ይሖዋን ወደሚያመልክበትና ወደሚያወድስበት ውጨኛ አደባባይ ያስገባል። ይህም ይሖዋን ‘ሌሊትና ቀን በመቅደሱ’ ስለሚያመልከው “እጅግ ብዙ ሕዝብ” የሚገልጸውን የሐዋርያው ዮሐንስ ራእይ ያስታውሰናል። በሁለቱም ራእዮች ውስጥ የዘንባባ ዝንጣፊዎች ታይተዋል። በሕዝቅኤል ራእይ ውስጥ የመግቢያውን ግድግዳዎች ለማስጌጫነት አገልግለዋል። በዮሐንስ ራእይ ውስጥ አምላኪዎቹ ይሖዋን ለማወደስና የኢየሱስን ንግሥና ለመቀበል በመቻላቸው የተሰማቸውን ደስታ ለመግለጽ በእጆቻቸው የዘንባባ ዝንጣፊዎች ይዘዋል። (ራእይ 7:9-15) በሕዝቅኤል ራእይ አገባብ 12ቱ የእስራኤል ነገዶች “ሌሎች በጎች”ን ያመለክታሉ። (ዮሐንስ 10:16፤ ከሉቃስ 22:28-30 ጋር አወዳድር።) መንግሥቱን በማወጅ ይሖዋን ለማወደስ በመቻላቸው ደስ ከሚሰኙት ሰዎች መካከል ናችሁ?
-