-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
1, 2. በሕዝቅኤል 47:1-12 ላይ እንደተገለጸው ሕዝቅኤል ምን ተመለከተ? (በመግቢያው ላይ ያለውን ሥዕል ተመልከት።)
ሕዝቅኤል ስለ ቤተ መቅደሱ ባየው ራእይ ላይ ሌላ አስደናቂ ነገር ተመለከተ፦ አንድ ጅረት ከቤተ መቅደሱ ወጥቶ ይፈስሳል። ሕዝቅኤል ይህን ኩልል ያለ ውኃ ተከትሎ ሲሄድ በዓይነ ሕሊናህ ይታይህ። (ሕዝቅኤል 47:1-12ን አንብብ።) ውኃው የሚመነጨው ከመቅደሱ ደፍ ሥር ነው፤ ከዚያም ቀስ ብሎ እየፈሰሰ በምሥራቁ በር አቅራቢያ ከቤተ መቅደሱ ግቢ ይወጣል። ሕዝቅኤልን የሚያስጎበኘው መልአክ ሕዝቅኤልን እየመራ ከቤተ መቅደሱ ውጭ ወሰደው፤ በሚሄዱበት ጊዜም ርቀቱን ይለካ ነበር። መልአኩ ሕዝቅኤልን በተደጋጋሚ በውኃው መካከል እንዲያልፍ አደረገው። ነቢዩም የውኃው ጥልቀት በፍጥነት እየጨመረ እንደሄደ አስተዋለ፤ ብዙም ሳይቆይ ውኃው በዋና ካልሆነ በስተቀር በእግር ሊሻገሩት የማይቻል ትልቅ ወንዝ ሆነ!
-
-
“ጅረቱ በሚፈስበት ቦታ ያለው ነገር ሁሉ በሕይወት ይኖራል”የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
-
-
4. (ሀ) ሕዝቅኤል በራእይ ያየው ወንዝ አይሁዳውያን የትኞቹን በረከቶች እንደሚያገኙ አረጋግጦላቸው መሆን አለበት? (ለ) መጽሐፍ ቅዱስ “ወንዝ” እና “ውኃ” የሚሉትን ቃላት የሚጠቀምበት መንገድ ይሖዋ ሕዝቦቹን እንደሚባርክ የሚያረጋግጥልን እንዴት ነው? (“የይሖዋን በረከት የሚያስገኙ ወንዞች” የሚለውን ሣጥን ተመልከት።)
4 በረከት የሚያስገኝ ወንዝ። አብዛኛውን ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ወንዝና ውኃ፣ ሕይወት ሰጪ የሆኑት የይሖዋ በረከቶች መፍሰሳቸውን ለማመልከት እንደ ምሳሌ ሆነው ያገለግላሉ። ሕዝቅኤል በራእይ ያየው ወንዝ ከቤተ መቅደሱ ወጥቶ ይፈስ ነበር፤ በመሆኑም ይህ ራእይ የአምላክ ሕዝቦች ከንጹሕ አምልኮ እስካልራቁ ድረስ ሕይወት ሰጪ የሆኑት የይሖዋ መንፈሳዊ በረከቶች ወደ እነሱ መፍሰሳቸውን እንደማያቆሙ አረጋግጦላቸው መሆን አለበት። እነዚህ በረከቶች ምን ነገሮችን ያካትታሉ? የአምላክ ሕዝቦች እንደ ቀድሞው ከካህናቱ መንፈሳዊ መመሪያ ያገኛሉ። በተጨማሪም በቤተ መቅደሱ ውስጥ መሥዋዕቶች ስለሚቀርቡ ኃጢአታቸው እንደሚሰረይላቸው መተማመን ይችላሉ። (ሕዝ. 44:15, 23፤ 45:17) በዚህ መንገድ ከቤተ መቅደሱ በሚወጣው ንጹሕ ውኃ የታጠቡ ያህል ዳግመኛ ንጹሕ ይሆናሉ።
-