-
‘በምድራችን’ ላይ የወረደው የይሖዋ በረከትመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
15. የአምላክን የሕይወት ዝግጅቶች የሚቀበለው ሁሉም ሰው አለመሆኑን የሚያሳየው ምንድን ነው? የእነዚህ ሰዎች መጨረሻስ ምንድን ነው?
15 እርግጥ ነው፣ በአሁኑ ጊዜ ሁሉ ሰው የሕይወትን መልእክት ለመቀበል ፈቃደኛ ይሆናል ወይም በክርስቶስ የሺህ ዓመት ግዛት ዘመን ከሙታን የሚነሱትም ሁሉም ተቀባዮች ይሆናሉ ማለት አይደለም። (ኢሳይያስ 65:20፤ ራእይ 21:8) መልአኩ የባሕሩ አንዳንድ ክፍሎች እንደማይፈወሱ ተናግሯል። እነዚህ በድን የሆኑ ረግረጋማ ቦታዎች “ጨው እንደሆኑ” ይኖራሉ። (ሕዝቅኤል 47:11) የይሖዋ ሕይወት ሰጪ ውኃ ከሚደርሳቸው የዘመናችን ሰዎችም መካከል ለመቀበል አሻፈረኝ የሚሉ አሉ። (ኢሳይያስ 6:10) በመንፈሳዊ በድንነታቸውና በበሽተኝነታቸው ለመኖር የመረጡ ሁሉ በአርማጌዶን ‘ጨው እንደሆኑ ይኖራሉ’ ማለትም ለዘላለም ይጠፋሉ። (ራእይ 19:11-21) ይህን ውኃ በታማኝነት ሲጠጡ የቆዩት ግን ከጥፋቱ ለመዳንና የዚህን ትንቢት የመጨረሻ ፍጻሜ ለመመልከት ተስፋ ሊያደርጉ ይችላሉ።
-
-
‘በምድራችን’ ላይ የወረደው የይሖዋ በረከትመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
18 በሺህ ዓመቱ ግዛት ማንኛውም አካላዊ፣ አእምሮአዊና ስሜታዊ ሕመም ይፈወሳል። አሕዛብ በምሳሌያዊው ዛፍ መፈወሳቸው የሚያመለክተው ይህንን ነው። በክርስቶስና በ144,000ዎቹ በኩል ላገኘናቸው ዝግጅቶች ምሥጋና ይድረስና “በዚያ የሚቀመጥ:- ታምሜያለሁ አይልም።” (ኢሳይያስ 33:24) ይህ ወንዙ ከፍተኛ መስፋፋት የሚያደርግበት ወቅት ይሆናል። ከዚህ ንጹሕ የሕይወት ውኃ ለሚጠጡት በሚልዮን፣ ምናልባትም በቢልዮን የሚቆጠሩ ከሙታን የሚነሱ ሰዎች በቂ እንዲሆን የበለጠ ጥልቀትና ስፋት ማግኘት ይኖርበታል። በሕዝቅኤል ራእይ ውስጥ ወንዙ ሙት ባሕርን ሲፈውስ ውኃው የደረሰበት አካባቢ ሁሉ ነፍስ ዘርቷል። ስለዚህ በገነት ውስጥ የሚኖሩ ወንዶችና ሴቶች በሙሉ በተዘረጋላቸው ቤዛዊ ጥቅሞች ካመኑ ከወረሱት አዳማዊ ሞት ተፈውሰው ሙሉ በሙሉ ሕያዋን ይሆናሉ። ራእይ 20:12 በዚያ ዘመን ከሙታን ለሚነሱት ጭምር የሚጠቅም ተጨማሪ እውቀትና ማስተዋል የሚሰጡ “ጥቅልሎች” እንደሚከፈቱ ይተነብያል። የሚያሳዝነው ግን በዚህ በገነት እንኳን ለመፈወስ እምቢተኛ የሚሆኑ አንዳንድ ሰዎች ይኖራሉ። ‘ጨው ሆነው እንዲቀሩ’ የሚደረጉት ማለትም ለዘላለም ጥፋት የሚዳረጉት እነዚህ ዓመፀኞች ናቸው።—ራእይ 20:15
-