-
‘በምድራችን’ ላይ የወረደው የይሖዋ በረከትመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
12. (ሀ) በሕዝቅኤል ራእይ ላይ የተገለጹት ዛፎች ያን ያህል ሊያፈሩ የቻሉት ለምንድን ነው? (ለ) በመጨረሻዎቹ ቀናት ውስጥ በእነዚህ ፍሬያማ ዛፎች የተወከለው ምንድን ነው?
12 በሕዝቅኤል ራእይ የታየው ወንዝ ሕይወትና ጤና አስገኝቷል። ሕዝቅኤል በወንዙ ዳርና ዳር ስለሚበቅሉት ዛፎች ሲነገረው “ቅጠሉም አይረግፍም፣ ፍሬውም አይጎድልም፤ . . . ፍሬውም ለመብል ቅጠሉም ለመድኃኒት ይሆናል” ተብሎ ነበር። እነዚህ ዛፎች እንዲህ ባለ አስደናቂ መንገድ ፍሬ የሚያፈሩት ለምንድን ነው? ‘ውኃው ከመቅደስ ስለሚወጣ ነው።’ (ሕዝቅኤል 47:12) እነዚህ ምሳሌያዊ ዛፎች የሰው ልጅ ወደ ፍጽምና እንዲመለስ አምላክ በኢየሱስ ቤዛዊ መሥዋዕት አማካኝነት ያደረጋቸውን ዝግጅቶች በሙሉ ያመለክታሉ። በአሁኑ ጊዜ በምድር ላይ ቅቡዓን ቀሪዎች መንፈሳዊ ምግብና ፈውስ በመስጠት ሥራ በግንባር ቀደምትነት ተሰልፈዋል። እነዚህ 144,000ዎች ሁሉም ሰማያዊ ሽልማታቸውን ከተቀበሉ በኋላ የክርስቶስ ተባባሪ ገዥዎች በመሆን ከሚያከናውኑት ክህነታዊ አገልግሎት የሚመነጩት ጥቅሞች ወደፊት ይዘረጋሉ፤ በመጨረሻም አዳማዊው ሞት ሙሉ በሙሉ ድል ይነሣል።—ራእይ 5:9, 10፤ 21:2-4
-
-
‘በምድራችን’ ላይ የወረደው የይሖዋ በረከትመጠበቂያ ግንብ—1999 | መጋቢት 1
-
-
17, 18. (ሀ) በራእይ 22:1, 2 ላይ ሕይወት ሰጪ የሆነው ወንዝ የተገለጸው እንዴት ነው? ትንቢቱ የመጀመሪያ ፍጻሜውን የሚያገኘው መቼ ነው? (ለ) በገነት ውስጥ የሕይወት ውኃ ወንዝ በስፋት መሰራጨት ያለበት ለምንድን ነው?
17 በዚያ ጊዜ ሕዝቅኤል የተመለከተው ወንዝ በጣም ከፍተኛ በሆነ የፈዋሽነት ኃይል የሚፈስስ ያህል ይሆናል። በራእይ 22:1, 2 ላይ የሚገኘው ትንቢት በዋነኛነት የሚፈጸመው በዚህ ጊዜ ነው:- “በአደባባይዋም መካከል ከእግዚአብሔርና ከበጉ ዙፋን የሚወጣውን እንደ ብርሌ የሚያንጸበርቀውን የሕይወትን ውኃ ወንዝ አሳየኝ። በወንዙም ወዲያና ወዲህ በየወሩ እያፈራ አሥራ ሁለት ፍሬ የሚሰጥ የሕይወት ዛፍ ነበረ፣ የዛፉም ቅጠሎች ለሕዝብ መፈወሻ ነበሩ።”
18 በሺህ ዓመቱ ግዛት ማንኛውም አካላዊ፣ አእምሮአዊና ስሜታዊ ሕመም ይፈወሳል። አሕዛብ በምሳሌያዊው ዛፍ መፈወሳቸው የሚያመለክተው ይህንን ነው። በክርስቶስና በ144,000ዎቹ በኩል ላገኘናቸው ዝግጅቶች ምሥጋና ይድረስና “በዚያ የሚቀመጥ:- ታምሜያለሁ አይልም።” (ኢሳይያስ 33:24) ይህ ወንዙ ከፍተኛ መስፋፋት የሚያደርግበት ወቅት ይሆናል። ከዚህ ንጹሕ የሕይወት ውኃ ለሚጠጡት በሚልዮን፣ ምናልባትም በቢልዮን የሚቆጠሩ ከሙታን የሚነሱ ሰዎች በቂ እንዲሆን የበለጠ ጥልቀትና ስፋት ማግኘት ይኖርበታል። በሕዝቅኤል ራእይ ውስጥ ወንዙ ሙት ባሕርን ሲፈውስ ውኃው የደረሰበት አካባቢ ሁሉ ነፍስ ዘርቷል። ስለዚህ በገነት ውስጥ የሚኖሩ ወንዶችና ሴቶች በሙሉ በተዘረጋላቸው ቤዛዊ ጥቅሞች ካመኑ ከወረሱት አዳማዊ ሞት ተፈውሰው ሙሉ በሙሉ ሕያዋን ይሆናሉ። ራእይ 20:12 በዚያ ዘመን ከሙታን ለሚነሱት ጭምር የሚጠቅም ተጨማሪ እውቀትና ማስተዋል የሚሰጡ “ጥቅልሎች” እንደሚከፈቱ ይተነብያል። የሚያሳዝነው ግን በዚህ በገነት እንኳን ለመፈወስ እምቢተኛ የሚሆኑ አንዳንድ ሰዎች ይኖራሉ። ‘ጨው ሆነው እንዲቀሩ’ የሚደረጉት ማለትም ለዘላለም ጥፋት የሚዳረጉት እነዚህ ዓመፀኞች ናቸው።—ራእይ 20:15
-