የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “አሁን ፍጻሜሽ ደርሷል”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • ሕዝቅኤል ፀጉሩን ሲላጭ።

      ሣጥን 6ሀ፦ “የራስህን ፀጉርና ጢምህን ተላጭ”

      7. ይሖዋ ለሕዝቅኤል ፀጉሩን ሦስት ቦታ እንዲከፋፍለውና በእያንዳንዱ ክፍል ላይ የተለያየ ነገር እንዲያደርግ የነገረው ለምን ነበር?

      7 ይሖዋ ለሕዝቅኤል የተላጨውን ፀጉሩን ሦስት ቦታ እንዲከፋፍለውና በእያንዳንዱ ክፍል ላይ የተለያየ ነገር እንዲያደርግ የነገረው ለምን ነበር? (ሕዝቅኤል 5:7-12⁠ን አንብብ።) ሕዝቅኤል ከኢየሩሳሌም ነዋሪዎች አንዳንዶቹ በከተማዋ ውስጥ እንደሚሞቱ ለማሳየት የፀጉሩን አንድ ክፍል “በከተማዋ ውስጥ” አቃጠለ። ሌሎቹ የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ከከተማዋ ውጭ እንደሚገደሉ ለማመልከት ደግሞ የፀጉሩን ሌላ ክፍል “በከተማዋ ዙሪያ” በሰይፍ መታ። ከዚያም የቀሩት የኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ወደተለያዩ ብሔራት እንደሚበተኑ ለማሳየት የመጨረሻውን የፀጉሩን ክፍል ለነፋስ በተነው፤ እነዚህ ሰዎች በሚበተኑበት ቦታ ሁሉ ‘ሰይፍ ያሳድዳቸዋል።’ ይህም ከጥፋቱ በሕይወት የተረፉት ሰዎች የትም ቦታ ቢሄዱ ሰላም እንደማያገኙ ያመለክታል።

  • “የራስህን ፀጉርና ጢምህን ተላጭ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
      • ሕዝቅኤል የተላጨውን ፀጉር አንድ ሦስተኛ ሲያቃጥል።

        ‘አቃጥለው’

        አንዳንዶች በከተማዋ ውስጥ ይሞታሉ

      • ሕዝቅኤል የተላጨውን ፀጉር አንድ ሦስተኛ በሰይፍ ሲመታ።

        ‘ምታው’

        አንዳንዶች ከከተማዋ ውጭ ይገደላሉ

      • ሕዝቅኤል የተላጨውን ፀጉር አንድ ሦስተኛ ሲበትን።

        ‘በትነው’

        አንዳንዶች ከጥፋቱ ያመልጣሉ፤ ግን ሰላም አያገኙም

  • “አሁን ፍጻሜሽ ደርሷል”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • 10 የአምላክ ቃል ወደፊት የሃይማኖት ተቋማት በሚጠፉበት ወቅት በርካታ የሐሰት ሃይማኖት ተከታዮች በሕይወት እንደሚተርፉ ይጠቁማል። በዚያን ጊዜ መሸሸጊያ ለማግኘት እንደሚራወጡት የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ሁሉ እነዚህ ሰዎችም በፍርሃት ተውጠው የሚደበቁበት ቦታ ለማግኘት ጥረት ያደርጋሉ። (ዘካ. 13:4-6፤ ራእይ 6:15-17) የእነዚህ ሰዎች ሁኔታ ከጥፋት ከተረፉ በኋላ ‘ለነፋስ የተበተኑትን’ የጥንቷ ኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ያስታውሰናል። በአንቀጽ 7 ላይ እንደተመለከትነው የጥንቷ ኢየሩሳሌም ነዋሪዎች ለጊዜው ሕይወታቸው ቢተርፍም ይሖዋ “እነሱን ለማሳደድ ሰይፍ” መዞባቸዋል። (ሕዝ. 5:2) በተመሳሳይም በሐሰት ሃይማኖት ላይ ከሚደርሰው ጥቃት የሚተርፉት ሰዎች የትም ቦታ ሄደው ለመሸሸግ ቢሞክሩ ከይሖዋ ሰይፍ ማምለጥ አይችሉም። ከሌሎቹ ፍየል መሰል ሰዎች ጋር አብረው በአርማጌዶን ይጠፋሉ።—ሕዝ. 7:4፤ ማቴ. 25:33, 41, 46፤ ራእይ 19:15, 18

      ምሥራቹን መናገራችንን ስለምናቆም እንደ “ዱዳ” እንሆናለን

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ