የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • “አሁን ፍጻሜሽ ደርሷል”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
    • 8. (ሀ) የሕዝቅኤል ትንቢታዊ ድራማ ምን የተስፋ ጭላንጭል ይዟል? (ለ) ስለ ‘ጥቂት ፀጉሮች’ የተነገረው ትንቢት ፍጻሜውን ያገኘው እንዴት ነበር?

      8 ይሁን እንጂ የሕዝቅኤል ትንቢታዊ ድራማ የተስፋ ጭላንጭልም የያዘ ነው። ይሖዋ ሕዝቅኤልን “ከፀጉሮቹ ላይ ጥቂት ወስደህ በልብስህ እጥፋት ቋጥራቸው” ብሎታል። (ሕዝ. 5:3) ይህ ትእዛዝ በብሔራት መካከል ከሚበተኑት አይሁዳውያን መካከል ጥቂቶች በሕይወት እንደሚተርፉ ያመለክታል። ከእነዚህ ‘ጥቂት ፀጉሮች’ ውስጥ አንዳንዶቹ ለ70 ዓመት የሚቆየው የባቢሎን ግዞት ሲያበቃ ወደ ኢየሩሳሌም ከሚመለሱት ግዞተኞች መካከል ይሆናሉ። (ሕዝ. 6:8, 9፤ 11:17) ታዲያ ይህ ትንቢት ፍጻሜውን አግኝቷል? በሚገባ! የባቢሎን ግዞት ካበቃ ከዓመታት በኋላ ነቢዩ ሐጌ ከተበተኑት አይሁዳውያን መካከል አንዳንዶቹ ወደ ኢየሩሳሌም እንደተመለሱ ዘግቧል። “የቀድሞውን ቤት [የሰለሞንን ቤተ መቅደስ] ያዩ ሽማግሌዎች” የተባሉት እነዚህ አይሁዳውያን ናቸው። (ዕዝራ 3:12፤ ሐጌ 2:1-3) ይሖዋ አስቀድሞ በገባው ቃል መሠረት ንጹሕ አምልኮ ሙሉ በሙሉ እንዳይጠፋ አድርጓል። በዚህ መጽሐፍ ምዕራፍ 9 ላይ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ስለተቋቋመበት መንገድ የሚገልጽ ተጨማሪ ማብራሪያ እናገኛለን።—ሕዝ. 11:17-20

  • “የራስህን ፀጉርና ጢምህን ተላጭ”
    የይሖዋ ንጹሕ አምልኮ መልሶ ተቋቋመ!
      • ሕዝቅኤል ከተላጨው ፀጉር ጥቂት ወስዶ በልብሱ እጥፋት ሲቋጥር።

        “ቋጥራቸው”

        አንዳንድ ግዞተኞች ወደ ኢየሩሳሌም ይመለሳሉ፤ ንጹሕ አምልኮም ሙሉ በሙሉ አይጠፋም

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ