የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዓለምን የለወጡ አራት ቃላት
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
    • 6 ይሁን እንጂ ብልጣሶር ገና ከዚህም የባሰ ነገር በማድረግ ሊሳለቅ ነው። “ንጉሡና መኳንንቶቹም ሚስቶቹና ቁባቶቹም . . . የወይን ጠጅ እየጠጡ ከወርቅና ከብር ከናስና ከብረት ከእንጨትና ከድንጋይ የተሠሩትን አማልክት አመሰገኑ።” (ዳንኤል 5:3, 4) ብልጣሶር የሐሰት አማልክቱን ከይሖዋ በላይ ከፍ ከፍ ማድረጉ ነበር! እንዲህ ዓይነቱ ዝንባሌ ደግሞ በባቢሎናውያን ዘንድ የተለመደ ነገር ይመስላል። በምርኮ የነበሩትን አይሁዳውያን ያንጓጥጧቸውና በአምልኳቸው ላይ ያላግጡ የነበረ ሲሆን ወደሚወዷት አገራቸው የመመለስ ምንም ተስፋ እንደሌላቸውም ይነግሯቸው ነበር። (መዝሙር 137:1-3፤ ኢሳይያስ 14:16, 17) ምናልባትም ይህ በመጠጥ የናወዘ ንጉሥ እነዚህን ምርኮኞች ማቃለሉና አምላካቸውን መሳደቡ ሴቶቹና ባለ ሥልጣኖቹ እንዲደነቁለት ሲል እንዲሁም በእነርሱ ፊት ኃያል መስሎ ለመታየት ያደረገው ሊሆን ይችላል።a ይሁን እንጂ ብልጣሶር ከፍ ያለ ሥልጣን እንዳለው ተሰምቶት ቢጀነንም እንኳ ይህ ስሜቱ ብዙም አልዘለቀም።

  • ዓለምን የለወጡ አራት ቃላት
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
    • a ተቀርጾ በተገኘ አንድ ጥንታዊ ጽሑፍ ላይ ንጉሥ ቂሮስ ብልጣሶርን በሚመለከት “በአገሪቱ ላይ [ገዥ] ሆኖ የተሾመው ደካማ ሰው ነው” ብሏል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ