-
ዓለምን የለወጡ አራት ቃላትየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
የግድግዳው ላይ ጽሕፈት
7, 8. የብልጣሶርን ግብዣ የሚያቋርጥ ምን ነገር ተከሰተ? ይህስ በንጉሡ ላይ ምን ውጤት ነበረው?
7 በመንፈስ አነሳሽነት የተጻፈው ዘገባ እንዲህ ይላል:- “በዚያም ሰዓት የሰው እጅ ጣቶች ወጥተው በንጉሡ ቤት በተለሰነው ግንብ ላይ በመቅረዙ አንጻር ጻፉ፤ ንጉሡም የሚጽፉትን ጣቶች አየ።” (ዳንኤል 5:5) እንዴት የሚያስፈራ ነገር ነው! ከየት መጣ ሳይባል አንድ እጅ ብቅ ብሎ ጥሩ ብርሃን በሚያገኘው ግድግዳ በኩል በአየር ላይ መንቀሳቀስ ጀመረ። ታዳሚዎቹ አፋቸውን ከፍተው ይህን እጅ ሲመለከቱ ድግሱ በምን ዓይነት ፀጥታ እንደሚዋጥ ገምት። እጁም በተለሰነው ግድግዳ ላይ አንድ ምሥጢራዊ መልእክት መጻፍ ጀመረ።b ይህ እጅግ ወሳኝና ፈጽሞ የማይረሳ ክስተት ነበር። ከዚህ የተነሣ እስከ ዛሬም ድረስ ሰዎች ፈጥኖ የሚመጣን ጥፋት ለማመልከት “የግድግዳው ላይ ጽሕፈት” የሚለውን መግለጫ ይጠቀማሉ።
-
-
ዓለምን የለወጡ አራት ቃላትየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
b ዳንኤል የተናገረው ይህ ዝርዝር ጉዳይ እንኳ ሳይቀር ትክክል መሆኑ ተረጋግጧል። አርኪኦሎጂስቶች የጥንቷ ባቢሎን የቤተ መንግሥት ግድግዳዎች በሸክላ የተሠሩና ከላይ የተለሰኑ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
-