-
ዓለምን የለወጡ አራት ቃላትየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
10. ጠቢባኑ በግድግዳው ላይ ያለውን ጽሕፈት ለመፍታት ያደረጉት ጥረት ውጤት ምን ሆነ?
10 ጠቢባኑ ሰፊው አዳራሽ ውስጥ ገብተው ተኮለኮሉ። ባቢሎን የሐሰት ሃይማኖቶች የሞሉባትና ብዙ ቤተ መቅደሶች የነበሯት ከተማ እንደመሆኗ መጠን እንዲህ ዓይነት ሰዎች ሞልተዋል። ልዩ ልዩ የድግምት ጽሑፎችን ትርጉም እንፈታለን የሚሉት እጅግ በርካታ እንደነበሩ ምንም ጥርጥር የለውም። እነዚህ ጠቢባን ከፊታቸው በተዘረጋው አጋጣሚ እጅግ ፈንጥዘው መሆን አለበት። በታወቁ ሰዎች ፊት ችሎታቸውን የሚያሳዩበት፣ የንጉሡን ሞገስ የሚያተርፉበትና ከፍተኛ ሥልጣን መጨበጥ የሚችሉበት አጋጣሚ ተከፍቶላቸዋል። ይሁን እንጂ እንዴት የሚያሳፍር ነው! “ጽሕፈቱንም ያነብቡ፣ ፍቺውንም ለንጉሡ ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም።”d—ዳንኤል 5:8
11. የባቢሎን ጠቢባን ጽሕፈቱን ሊያነቡት ያልቻሉት ለምን ሊሆን ይችላል?
11 የባቢሎን ጠቢባን ለመረዳት የተቸገሩት ጽሕፈቱን ራሱን ማለትም ፊደላቱን ስለመሆኑ በእርግጠኛነት መናገር አይቻልም። ፊደላቱ የማይታወቁ ሆነው አግኝተዋቸው ቢሆን ኖሮ እነዚህ ይሉኝታ የሌላቸው ሰዎች ንጉሡን ለመደለል የራሳቸውን ታሪክ ፈጥረው ሊናገሩ የሚችሉበት አጋጣሚ ይኖራቸው ነበር። ሌላው አማራጭ ደግሞ ፊደላቱ በቀላሉ የሚነበቡ ሆነው ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ እንደ አረማይክና ዕብራይስጥ ያሉት ቋንቋዎች የሚጻፉት ካለ አናባቢ ስለነበር እያንዳንዱ ቃል የተለያየ ትርጉም ሊኖረው ይችላል። እንደዚያ ከሆነ እነዚህ ጠቢባን የትኛውን ቃል ለማለት እንደተፈለገ ለመወሰን ተቸግረው መሆን አለበት። የትኛውን ቃል ለማለት እንደተፈለገ ማወቅ ቢችሉ እንኳ ፍችውን ለመናገር የቃሎቹን ትርጉም መረዳት ተስኗቸው ሊሆን ይችላል። ያም ሆነ ይህ አንድ ነገር ተረጋግጧል። የባቢሎን ጠቢባን ምንም አልፈየዱም!
-
-
ዓለምን የለወጡ አራት ቃላትየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
d ቢብሊካል አርኪኦሎጂ ሪቪው የተባለው መጽሔት እንዲህ ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል:- “ባቢሎናውያን ኤክስፐርቶች በሺህ የሚቆጠሩ የገድ ምልክቶችን በዝርዝር አስፍረዋል። . . . ብልጣሶር በግድግዳው ላይ ያለውን ጽሑፍ ትርጉም ለማወቅ በጠየቀ ጊዜ የባቢሎን ጠቢባን እነዚህን የገድ ኢንሳይክለፒዲያዎች እንዳገላበጡ ምንም ጥርጥር የለውም። ይሁን እንጂ የፈየዱላቸው አንዳች ነገር አልነበረም።”
-