-
ፍጻሜያቸውን ያገኙ ትንቢቶችመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
22. ከዓለም ኃያላን መፈራረቅ ጋር በተያያዘ ስለ የትኛው ተጨማሪ የዓለም ኃይል ትንቢት ተነግሯል?
22 በዳንኤል ምዕራፍ 7 ላይም ገና ከረጅም ጊዜ በኋላ ፍጻሜውን ማግኘት የነበረበት ተመሳሳይ ትንቢት ተገልጿል። የባቢሎናውያን የዓለም ኃይል በአንበሳ፣ የፋርስ በድብ እንዲሁም የግሪክ ጀርባዋ ላይ አራት ክንፎች ባሏት ባለ አራት ራስ ነብር ተመስለዋል። ከዚያም ዳንኤል ‘የምታስፈራና የምታስደነግጥ እጅግም የበረታች አሥር ቀንዶችም የነበሩዋት’ አውሬ ተመለከተ። (ዳንኤል 7:2-7) አራተኛዋ አውሬ ጥላ የሆነችለት ኃያል የነበረው የሮም አገዛዝ ብቅ ማለት የጀመረው ዳንኤል ትንቢቱን ከጻፈ ሦስት መቶ ዘመናት ገደማ ቆይቶ ነው።
-
-
ፍጻሜያቸውን ያገኙ ትንቢቶችመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
24, 25. (ሀ) የአውሬው አሥር ቀንዶች ብቅ ያሉት እንዴት ነው? (ለ) ዳንኤል በአውሬው ቀንዶች መካከል ስለሚደረገው ስለየትኛው ትግል አስቀድሞ ተመልክቷል?
24 ይሁን እንጂ ስለዚህ ግዙፍ የሆነ አውሬ አሥር ቀንዶችስ ምን ማለት ይቻላል? መልአኩ እንዲህ ብሏል:- “አሥሩም ቀንዶች ከዚያ መንግሥት የሚነሡ አሥር ነገሥታት ናቸው፤ ከእነርሱም በኋላ ሌላ ይነሣል፣ እርሱም ከፊተኞች የተለየ ይሆናል፣ ሦስቱን ነገሥታት ያዋርዳል።” (ዳንኤል 7:24) ይህስ ፍጻሜውን ያገኘው እንዴት ነው?
25 በአምስተኛው መቶ ዘመን እዘአ የሮማ ግዛት እየተዳከመ መሄድ ሲጀምር ወዲያውኑ በሌላ የዓለም ኃይል አልተተካም። ከዚህ ይልቅ ወደተለያዩ “አሥር መንግሥት” ተከፋፈለ። በመጨረሻም የብሪታንያ ግዛት ተቀናቃኝ የነበሩትን ሦስቱን የስፔይን፣ የፈረንሳይና የኔዘርላንድስን መንግሥታት ድል በማድረግ ዋና የዓለም ኃይል ሆነ። በዚህ መንገድ አዲስ የመጣው ‘ቀንድ’ ሌሎቹን “ሦስቱን ነገሥታት” አዋርዷቸዋል።
-