-
መሲሑ የሚመጣበት ጊዜ ታወቀየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
25 ኃጢአትና ሞት የሰውን ልጅ ፍዳ ማስቆጠራቸውን ቢቀጥሉም ኢየሱስ በመሞትና ሰማያዊ ሕይወት አግኝቶ ከሞት በመነሳት ትንቢቱ ፍጻሜውን እንዲያገኝ አድርጓል። ‘መተላለፍን አስቀርቷል፣ ኃጢአትን ወደ ፍጻሜው አምጥቷል፣ በደልንም አስተሰርዮአል፣ ጽድቅንም አግብቷል።’ አምላክ፣ አይሁዳውያን ኃጢአተኞች መሆናቸውን ያጋለጠውንና የኮነናቸውን ሕግ አስወግዶት ነበር። (ሮሜ 5:12, 19, 20፤ ገላትያ 3:13, 19፤ ኤፌሶን 2:14, 15፤ ቆላስይስ 2:13, 14) ከዚህ በኋላ ንስሐ የሚገቡ ኃጢአተኞች በደላቸው ሊሰረዝላቸውና ቅጣታቸውም ሊቀር ይችላል። እምነት ለሚያሳዩ ሰዎች በመሲሑ የማስተሠርያ መሥዋዕት አማካኝነት ከአምላክ ጋር መታረቅ የሚችሉበት መንገድ ተከፍቶላቸው ነበር። ‘በክርስቶስ ኢየሱስ የሚገኘውን የዘላለም ሕይወት’ ለማግኘት ተስፋ ሊያደርጉ ይችላሉ።—ሮሜ 3:21-26፤ 6:22, 23፤ 1 ዮሐንስ 2:1, 2
-
-
መሲሑ የሚመጣበት ጊዜ ታወቀየዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
-
-
27. የተቀባው ‘ቅድስተ ቅዱሳን’ ምንድን ነው? እንዴትስ?
27 በተጨማሪም ትንቢቱ ‘ቅድስተ ቅዱሳኑ’ እንደሚቀባ ተናግሯል። ይህ የሚያመለክተው በኢየሩሳሌም የሚገኘው ቤተ መቅደስ ቅድስተ ቅዱሳን ወይም ውስጠኛ ክፍል መቀባቱን አይደለም። እዚህ ላይ ‘ቅድስተ ቅዱሳን’ የሚለው ቃል የሚያመለክተው የአምላክን ሰማያዊ መቅደስ ነው። በዚያም ኢየሱስ የሰብዓዊ ሕይወቱን ዋጋ ለአባቱ አቅርቧል። ኢየሱስ በ29 እዘአ መጠመቁ በምድራዊው መገናኛ ድንኳን በኋላም ቤተ መቅደስ ውስጥ በነበረው ቅድስተ ቅዱሳን የሚወከለው ሰማያዊ ማለትም መንፈሳዊ ሁኔታ እንዲቀባ ወይም ለሥራ የተለየ እንዲሆን አድርጓል።—ዕብራውያን 9:11, 12
አምላክ ማረጋገጫ የሰጠበት ትንቢት
28. ‘ራእይንና ነቢይን ማተሙ’ ምን ትርጉም አለው?
28 መልአኩ ገብርኤል የተናገረው መሲሐዊ ትንቢት ‘ራእይንና ነቢይን ስለ ማተምም’ ይገልጻል። ይህም ማለት መሲሑ በመሥዋዕቱ፣ በትንሣኤውና በሰማይ በመገኘቱ እንዲሁም በ70ኛው ሳምንት በተከናወኑት ነገሮች አማካኝነት እንደሚፈጽማቸው የተነገሩትን ጨምሮ መሲሑን የሚመለከቱት ሁሉም ትንቢቶች መለኮታዊ ማረጋገጫ እንዳላቸው በሚያሳይ መንገድ ታትመዋል፣ ፍጻሜያቸውን ያገኛሉ፣ አመኔታም የሚጣልባቸው ይሆናሉ ማለት ነው። ራእይው መታተሙ ለመሲሑ ብቻ የተወሰነ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው። ፍጻሜውን የሚያገኘው በመሲሑና አምላክ በእርሱ አማካኝነት በሚያከናውነው ሥራ ይሆናል። የራእይውን ትክክለኛ ማብራሪያም ማግኘት የምንችለው በትንቢት ከተነገረለት መሲሕ ብቻ ይሆናል። ታትሟልና ሌላ ትርጉሙን ሊፈታልን የሚችል አይኖርም።
-