-
ፍጻሜያቸውን ያገኙ ትንቢቶችመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
32. በዳንኤል ትንቢት መሠረት የኢየሱስ ምድራዊ አገልግሎት ለምን ያህል ጊዜ የሚዘልቅ ነው? ይህ ጊዜ ሲፈጸምስ ምን ነገር ይከናወናል?
32 ትንቢቱ በመጨመር እንዲህ ይላል:- “ከስድሳ ሁለት [የዓመታት] ሳምንትም በኋላ የተቀባው ይገደላል።” አክሎም “እርሱም ከብዙ ሰዎች ጋር ጽኑ ቃል ኪዳን ለአንድ ሳምንት [ሰባት ዓመታት] ያደርጋል፤ በሳምንቱም እኩሌታ መሥዋዕቱንና ቁርባኑን ያስቀራል።” (ዳንኤል 9:26, 27, ኤቢ) ከዚህ ትንቢት ጋር በሚስማማ መንገድ ኢየሱስ የሄደው ወደ ‘ብዙዎች’ ማለትም ወደ ሥጋዊ አይሁዳውያን ብቻ ነበር። በተወሰነው የቅዱስ ጽሑፉ ክፍል ያምኑ ለነበሩት ነገር ግን ከዋናው የአይሁድ እምነት ተገንጥለው የራሳቸውን ወገን ለመሠረቱት ሳምራውያንም የሰበከባቸው ወቅቶች ነበሩ። ከዚያም ‘በሳምንቱ እኩሌታ’ ማለትም ለሦስት ዓመት ተኩል ከሰበከ በኋላ ሕይወቱን መሥዋዕት አድርጎ ሰጠ፣ በሌላ አባባል ‘ተቆረጠ።’ ይህም የሙሴ ሕግ ከነመሥዋዕቱና ቁርባኑ ወደ ፍጻሜው እንደመጣ የሚያሳይ ነበር። (ገላትያ 3:13, 24, 25) በመሆኑም ኢየሱስ በሞቱ ‘መሥዋዕቱና ቁርባኑ’ እንዲቀር አድርጓል።
-
-
ፍጻሜያቸውን ያገኙ ትንቢቶችመጽሐፍ ቅዱስ—የአምላክ ቃል ነው ወይስ የሰው?
-
-
34. ከዳንኤል ትንቢት ጋር በሚስማማ መንገድ ሥጋዊ እስራኤላውያን መሲሑን ለመቀበል አሻፈረን በማለታቸው ምን ደሶባቸዋል?
34 የአይሁድ ብሔር ኢየሱስን አልቀበልም በማለቱና እንዲገደል በማሴሩ ሮማውያን መጥተው በ70 እዘአ ኢየሩሳሌምን ሲያጠፉ ይሖዋ ሳያስጥላቸው ቀርቷል። በዚህ መንገድ የሚከተሉት የዳንኤል ቃላት ፍጻሜያቸውን አግኝተዋል:- “የሚመጣውም ሌላው አለቃ ሕዝብ ከተማይቱንና መቅደሱን ያጠፋሉ፤ ፍጻሜውም በጎርፍ ይሆናል፣ እስከ መጨረሻም ድረስ በጦርነት ይሆናል።” (ዳንኤል 9:26 ኤቢ) ይህ ሁለተኛው “አለቃ” ኢየሩሳሌምን በ70 እዘአ ያጠፋው ሮማዊው ጄኔራል ቲቶ ነው።
-