-
“ባለ ሐር ፀጉሯ የሶርያ በረሃ እመቤት”መጠበቂያ ግንብ—1999 | ጥር 15
-
-
በ269 እዘአ የሮማን አገዛዝ የሚቀናቀን አስመሳይ መንግሥት በግብጽ በተነሣ ጊዜ ዘኖቢያ ንጉሣዊ ሥልጣኗን የምታሰፋበት አመቺ አጋጣሚ አገኘች። የዘኖቢያ ሠራዊት በፍጥነት ወደ ግብፅ በመዝመት ዓማፂዎቹን ደምስሶ አገሪቱን ተቆጣጠረ። ራሷን የግብጽ ንግሥት ብላ በመሰየም ስሟ ያለበት ሳንቲም አስቀረጸች። በዚህ ጊዜ የመንግሥቷ ግዛት ከአባይ ወንዝ እስከ ኤፍራጥስ ወንዝ ድረስ ሆነ። “የደቡብ ንጉሥ” ሆና በመጽሐፍ ቅዱሱ የዳንኤል ትንቢት ውስጥ የተጠቀሰችው በዚህ ወቅት ነበር። ምክንያቱም መንግሥቷ ከዳንኤል የትውልድ አገር በስተደቡብ ያለውን ቦታ ተቆጣጥሮ ነበር። (ዳንኤል 11:25, 26) ከዚህም ሌላ አብዛኛውን የትንሿን እስያ ክፍል ተቆጣጥራ ነበር።
-
-
“ባለ ሐር ፀጉሯ የሶርያ በረሃ እመቤት”መጠበቂያ ግንብ—1999 | ጥር 15
-
-
አንድ ንጉሠ ነገሥት በዘኖቢያ ላይ ‘ልቡን አነሣ’
በ270 እዘአ ኦሬሊየን የሮም ንጉሠ ነገሥት ሆነ። ጭፍሮቹ በተሳካ ሁኔታ በሰሜን የነበሩትን ኋላቀር ወገኖች መመከትና ቀጥተው መመለስ ችለው ነበር። በ271 እዘአ ደግሞ በዳንኤል ትንቢት ውስጥ የተገለጸውን ‘የሰሜን ንጉሥ’ በመወከል ኦሬሊየን በዘኖቢያ የሚወከለውን ‘የደቡብ ንጉሥ’ ለመውጋት ‘ኃይሉንም ልቡንም አነሣ።’ (ዳንኤል 11:25) ኦሬሊየን የተወሰነውን ሠራዊቱን በቀጥታ ወደ ግብጽ በመላክ ዋናውን ሠራዊቱን በትንሿ እስያ በኩል ወደ ምሥራቅ ላከ።
የደቡብ ንጉሥ ማለትም በዘኖቢያ የሚመራው አገዛዝ ዜብዳስና ዜባይ በተባሉ ሁለት ጄኔራሎች በመመራት “በታላቅና በብዙ ሠራዊት ሆኖ” ኦሬሊየንን ለመግጠም ተነሣ። (ዳንኤል 11:25) ነገር ግን ኦሬሊየን ግብጽን በቁጥጥሩ ሥር ካደረገ በኋላ ወደ ትንሿ እስያና ወደ ሶርያ መዝመት ጀመረ። ዘኖቢያ (ዛሬ ሆምስ በምትባለው) በኤመሳ ድል ተነስታ ወደ ፓልሚራ አፈገፈገች።
ኦሬሊየን ፓልሚራን በቁጥጥሩ ሥር ሲያውል ዘኖቢያ እርዳታ እንደምታገኝ በማሰብ ከወንድ ልጁዋ ጋር ወደ ፋርስ ሸሸች። ይሁን እንጂ ገና የኤፍራጥስን ወንዝ ሳትሻገር ሮማውያን ማረኳት። የፓልሚራ ሰዎች ከተማቸውን በ272 እዘአ ለወራሪዎች አስረከቡ። ኦሬሊየን የከተማዋን ነዋሪዎች አባብሎ በመያዝ ከፀሐይ ቤተ መቅደስ የተወሰዱ ጣዖታትን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የተለያየ ቁሳቁስ ዘርፎ ወደ ሮም አሻግሮ ነበር። የሮማው ንጉሠ ነገሥት ዘኖቢያን በሕይወት ካስመጣት በኋላ በ274 እዘአ በሮም ከተማ የተካሄደውን የድል ሰልፍ እንድታደምቅ አድርጓል። ቀሪ የሕይወት ዘመኗን የሮማ እመቤት ሆና አሳልፋለች።
የበረሃዋ ከተማ ተደመሰሰች
ኦሬሊየን ፓልሚራን ከተቆጣጠረ ከጥቂት ወራት በኋላ የፓልሚራ ሰዎች በዚያ አካባቢ የቀረውን ጠባቂ ጦር ጨፈጨፉት። የዚህ ዓመፅ ወሬ ኦሬሊየን ጆሮ በደረሰ ጊዜ ወታደሮቹ ወደ መጡበት እንዲመለሱ ትእዛዝ ሰጠ። በዚህ ጊዜ በሕዝቡ ላይ ከፍተኛ የበቀል እርምጃ ወስደዋል። ከምሕረት የለሹ ጭፍጨፋ ያመለጡት በባርነት ተወሰዱ። ያች የተከበረች ከተማ ዳግም እንደማትጠገን ሆና ተበዘበዘች፣ ወደመች። ያች ሞቅ ደመቅ ያለች ከተማ ድሮ ወደነበረችበት ሁኔታዋ ማለትም ‘በምድረ በዳ እንደነበረችው ተድሞር’ ሆነች።
ዘኖቢያ ሮምን በተቋቋመች ጊዜ እርሷም ሆነች ንጉሠ ነገሥቱ ኦሬሊየን ባይታወቃቸውም ‘የደቡብ ንጉሥና’ ‘የሰሜን ንጉሥ’ በመሆን ከ800 ዓመታት በፊት የይሖዋ ነቢይ በዝርዝር በመዘገበው ትንቢት ውስጥ ያሉት ነገሮች በከፊል ፍጻሜያቸውን እንዲያገኙ አድርገዋል። (ዳንኤል ምዕራፍ 11) ዘኖቢያ በማራኪ ስብዕናዋ የብዙዎችን አድናቆት አትርፋለች። ይሁን እንጂ ከሁሉ ይበልጥ ጉልህ ሥፍራ የሚሰጠው በዳንኤል ትንቢት ውስጥ የተጠቀሰውን ፖለቲካዊ ኃይል በመወከል የተጫወተችው ሚና ነው። ግዛቷ ከአምስት ዓመት በላይ አልዘለቀም። የዘኖቢያ መንግሥት መዲና የነበረችው ፓልሚራ ዛሬ አንዲት ትንሽ መንደር ናት። ኃያል የነበረው የሮማ ንጉሠ ነገሥት ግዛትም ሳይቀር ጠፍቶ ዛሬ ላሉት መንግሥታት ቦታውን ለቅቋል። የእነዚህ ኃይላት የወደፊት ዕጣ ምን ይሆናል? የእነርሱም ዕጣ ፋንታ በእርግጠኝነት ፍጻሜውን በሚያገኘው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ላይ የተመካ ነው።—ዳንኤል 2:44
-