የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ባላንጣዎቹ ነገሥታት ፍጻሜያቸው ቀርቧል
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
    • 3, 4. ‘ቃል ኪዳኑን የሚበድሉት’ እነማን ናቸው? ከሰሜኑ ንጉሥ ጋርስ ምን ዓይነት ግንኙነት ነበራቸው?

      3 የአምላክ መልአክ “[የሰሜኑም ንጉሥ] ቃል ኪዳኑን የሚበድሉትንም በማታለል ያስታል” ካለ በኋላ ጨምሮ እንዲህ ብሏል:- “ነገር ግን አምላካቸውን የሚያውቁ ሕዝብ ይበረታሉ፣ ያደርጋሉም። በሕዝቡም መካከል ያሉ ጥበበኞች ብዙ ሰዎችን ያስተምራሉ፤ ነገር ግን በሰይፍና በእሳት ነበልባል በምርኮና በመበዝበዝ ብዙ ዘመን ይወድቃሉ።”—ዳንኤል 11:32, 33

  • ባላንጣዎቹ ነገሥታት ፍጻሜያቸው ቀርቧል
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
    • 5, 6. ‘አምላካቸውን የሚያውቁ ሕዝብ’ የተባሉት እነማን ናቸው? በሰሜኑ ንጉሥ ሥር ምን ዓይነት ሁኔታ አሳልፈዋል?

      5 “አምላካቸውን የሚያውቁ ሕዝብ” እና “ጥበበኛ” ስለተባሉት እውነተኛ ክርስቲያኖችስ ምን ማለት ይቻላል? በሰሜኑ ንጉሥ ግዛት ሥር የነበሩት ክርስቲያኖች ‘በበላይ ላሉ ባለ ሥልጣኖች ባግባቡ ይገዙ’ የነበረ ቢሆንም የዓለም ክፍል አልሆኑም። (ሮሜ 13:1፤ ዮሐንስ 18:36) “የቄሣርን ለቄሣር” በማስረከብ በኩል ጠንቃቆች የነበሩ ቢሆንም ‘የእግዚአብሔርንም ለእግዚአብሔር’ ከመስጠት ወደኋላ አላሉም። (ማቴዎስ 22:21) በዚህም ምክንያት ንጹህ አቋማቸውን ለመጠበቅ ፈታኝ ሁኔታ ገጥሟቸዋል።—2 ጢሞቴዎስ 3:12

      6 ከዚህ የተነሣ እውነተኛ ክርስቲያኖች ‘ወድቀዋልም፤’ ‘በርትተዋልም።’ እንደ ወደቁ ተደርገው የተገለጹት ከደረሰባቸው ከባድ ስደት የተነሣ ሲሆን እንዲያውም አንዳንዶቹ ተገድለዋል። ይሁን እንጂ አብዛኞቹ የታመኑ ሆነው በመገኘታቸው በርትተዋል። ልክ እንደ ኢየሱስ ዓለምን አሸንፈዋል። (ዮሐንስ 16:33) ከዚህም በላይ በእስር ቤቶች ወይም በማጎሪያ ካምፖች ውስጥ ቢጣሉም ፈጽሞ ስብከታቸውን አላቆሙም። በዚህ መንገድ ‘ብዙ ሰዎችን አስተምረዋል።’ በሰሜኑ ንጉሥ ቁጥጥር ሥር በነበሩት በአብዛኛዎቹ አገሮች ስደት የነበረ ቢሆንም የይሖዋ ምሥክሮች ቁጥር ጨምሯል። ‘ጥበበኞች’ የተባሉት ሰዎች ላሳዩት ታማኝነት ምስጋና ይግባውና በእነዚህ አገሮች ውስጥ ቁጥሩ እያደገ የሚሄድ “እጅግ ብዙ ሕዝብ” ብቅ ብሏል።—ራእይ 7:9-14

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ