የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ባላንጣዎቹ ነገሥታት ፍጻሜያቸው ቀርቧል
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
    • በፍጻሜው ዘመን የሚታይ ‘ግፊያ’

      15. የደቡቡ ንጉሥ ከሰሜኑ ንጉሥ ጋር ‘የተጋፋው’ እንዴት ነው?

      15 መልአኩ “በፍጻሜ ዘመንም የደቡብ ንጉሥ ከእርሱ ጋር ይዋጋል [“ይጋፋል፣” NW]” ሲል ለዳንኤል ነግሮታል። (ዳንኤል 11:40ሀ) ‘በፍጻሜው ዘመን’ የደቡቡ ንጉሥ የሰሜኑን ንጉሥ ‘ተጋፍቶታልን?’ (ዳንኤል 12:4, 9) አዎን፣ ተጋፍቶታል። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ በወቅቱ የሰሜን ንጉሥ በነበረችው ጀርመን ላይ የተጣለው ቅጣት አዘል የሰላም ስምምነት ለበቀል የሚያነሳሳ ‘የመጋፋት’ እርምጃ ነበር። የደቡቡ ንጉሥ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ድል ከተቀዳጀ በኋላ አስፈሪውን የኑክሌር ጦር መሣሪያውን በተቀናቃኙ ላይ ከማነጣጠሩም ሌላ እርሱን የሚቃወም የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) የተባለ ኃያል ወታደራዊ ኅብረት አደራጅቷል። የኔቶን ተግባር በተመለከተ አንድ እንግሊዛዊ ታሪክ ጸሐፊ እንዲህ ብለዋል:- “ለአውሮፓ ሰላም አስጊ እንደሆነች ተደርጋ የምትታሰበውን የሶቪየት ኅብረትን መስፋፋት ለመግታት የሚያገለግል ዋነኛ መሣሪያ ነው። ለ40 ዓመታት ያህል ተልእኮውን በተሳካ መንገድ አከናውኗል።” የቀዝቃዛው ጦርነት ዘመን እየቀጠለ ሲሄድ የደቡቡ ንጉሥ ‘ግፊያ’ እጅግ ዘመናዊ በሆነ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ስለላ ማካሄድን እንዲሁም ዲፕሎማሲያዊና ወታደራዊ ትንኮሳን የሚጨምር ሆኗል።

      16. የሰሜኑ ንጉሥ ለደቡቡ ንጉሥ ግፊያ ምን ምላሽ ሰጠ?

      16 የሰሜኑ ንጉሥ ምላሽ ምን ነበር? “የሰሜንም ንጉሥ ከሰረገሎችና ከፈረሰኞች ከብዙም መርከቦች ጋር እንደ ዐውሎ ነፋስ ይመጣበታል፤ ወደ አገሮችም ይገባል፣ ይጎርፍማል፣ ያልፍማል።” (ዳንኤል 11:40ለ) የሰሜኑ ንጉሥ መስፋፋት በመጨረሻዎቹ ቀናት በጉልህ ተንጸባርቋል። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት የናዚ “ንጉሥ” አዋሳኝ ወደሆኑት የአካባቢው አገሮች ዘምቷል። በጦርነቱ ማብቂያ ላይ ደግሞ በእርሱ ፋንታ የተነሣው “ንጉሥ” ጠንካራ ግዛት ገንብቷል። በቀዝቃዛው ጦርነት ወቅት የሰሜን ንጉሥ ተቀናቃኙን በእጅ አዙር ጦርነትና በአፍሪካ፣ በእስያ እንዲሁም በላቲን አሜሪካ በተደረጉ ዓመፆች አማካኝነት ተዋግቶታል። በእውነተኛ ክርስቲያኖች ላይ ስደት በማድረስ ሥራቸውን ቢገድበውም ጨርሶ ማስቆም ሳይችል ቀርቷል። የወሰዳቸው ወታደራዊና ፖለቲካዊ እርምጃዎች በርካታ አገሮችን በቁጥጥሩ ሥር ለማድረግ አስችሎታል። መልአኩም ስለዚሁ ጉዳይ በትክክል ተንብዮአል:- “ወደ መልካሚቱም [“ጌጧ፣” NW] ምድር [ወደ ይሖዋ ሕዝቦች መንፈሳዊ ይዞታ] ይገባል፣ ብዙ አገሮችም ይወድቃሉ።”—ዳንኤል 11:41ሀ

  • ባላንጣዎቹ ነገሥታት ፍጻሜያቸው ቀርቧል
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
    • [በገጽ 279 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

      የደቡቡ ንጉሥ ‘ግፊያ ’ እጅግ ዘመናዊ በሆነ ቴክኖሎጂ የተደገፈ ስለላ ማካሄድንና ወታደራዊ ማስፈራሪያዎችን ያካትታል

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ