-
“የጽድቅን ጎዳና እንዲከተሉ ብዙ ሰዎችን” መርዳትመጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022 | መስከረም
-
-
6. እጅግ ብዙ ሕዝብ ታላቁን መከራ ካለፉ በኋላ ምን ይከናወናል? አብራራ። (በተጨማሪም በዚህ መጽሔት ውስጥ የሚገኘውን ስለ ምድራዊ ትንሣኤ የሚገልጸውን “የአንባቢያን ጥያቄዎች” ተመልከት።)
6 ዳንኤል 12:2ን አንብብ። እጅግ ብዙ ሕዝብ ይህን የጭንቀት ጊዜ ካለፉ በኋላ ምን ይከናወናል? ይህ ትንቢት ቀደም ሲል እናስብ እንደነበረው በመጨረሻዎቹ ቀናት ውስጥ የሚከናወነውን ምሳሌያዊ ትንሣኤ ማለትም የአምላክ አገልጋዮች በመንፈሳዊ ማንሰራራታቸውን የሚያመለክት አይደለም።c ከዚህ ይልቅ ይህ ሐሳብ የሚናገረው በመጪው አዲስ ዓለም ውስጥ ስለሚከናወነው የሙታን ትንሣኤ ነው። እዚህ መደምደሚያ ላይ እንድንደርስ ያደረገን ምንድን ነው? “አፈር” የሚለው ቃል በኢዮብ 17:16 ላይ ‘መቃብርን’ ለማመልከት ተሠርቶበታል። በመሆኑም ዳንኤል 12:2 የሚናገረው የመጨረሻዎቹ ቀናት ካበቁና የአርማጌዶን ጦርነት ከተካሄደ በኋላ ስለሚኖረው የሙታን ትንሣኤ እንደሆነ መረዳት እንችላለን።
7. (ሀ) አንዳንዶች “ለዘላለም ሕይወት” ይነሳሉ ሲባል ምን ማለት ነው? (ለ) ይህ ትንሣኤ “የተሻለ ትንሣኤ” የሆነው በምን መንገድ ነው?
7 ይሁንና ዳንኤል 12:2 አንዳንዶች “ለዘላለም ሕይወት” እንደሚነሱ ሲናገር ምን ማለቱ ነው? ትንሣኤ ከሚያገኙት መካከል ይሖዋንና ኢየሱስን የሚያውቁ ወይም ማወቃቸውን የሚቀጥሉ እንዲሁም በ1,000 ዓመቱ ወቅት እነሱን የሚታዘዙ ሰዎች በመጨረሻ የዘላለም ሕይወት ያገኛሉ ማለት ነው። (ዮሐ. 17:3) ይህ በጥንት ጊዜ ከሞት የተነሱ አንዳንድ ሰዎች ካገኙት ትንሣኤ “የተሻለ ትንሣኤ” ይሆናል። (ዕብ. 11:35) ለምን? ምክንያቱም ከሞት የተነሱት እነዚያ ፍጹማን ያልሆኑ ሰዎች በድጋሚ ሞተዋል።
8. ሌሎች “ለነቀፋና ለዘላለማዊ ውርደት” ይነሳሉ ሲባል ምን ማለት ነው?
8 ሆኖም ከሞት ከተነሱት ሰዎች መካከል ይሖዋ ያዘጋጀውን የትምህርት መርሐ ግብር የማይቀበሉ ይኖራሉ። የዳንኤል ትንቢት አንዳንዶች “ለነቀፋና ለዘላለማዊ ውርደት” እንደሚነሱ ይገልጻል። እነዚህ ሰዎች የዓመፀኝነት መንፈስ ስለሚያሳዩ ስማቸው በሕይወት መጽሐፍ ውስጥ አይጻፍም፤ የዘላለም ሕይወትም አያገኙም። ከዚህ ይልቅ “ዘላለማዊ ውርደት” ወይም ጥፋት ይደርስባቸዋል። ስለዚህ ዳንኤል 12:2 የሚናገረው ትንሣኤ ያገኙ ሰዎች በሙሉ ከሞት ከተነሱ በኋላ በሚያደርጉት ነገር መሠረት የሚጠብቃቸውን የመጨረሻ ዕጣ ነው።d (ራእይ 20:12) አንዳንዶች የዘላለም ሕይወት ያገኛሉ፤ ሌሎች ደግሞ አያገኙም።
-
-
“የጽድቅን ጎዳና እንዲከተሉ ብዙ ሰዎችን” መርዳትመጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022 | መስከረም
-
-
a ይህ ርዕስ በዳንኤል 12:2, 3 ላይ ከተጠቀሰው መጠነ ሰፊ የትምህርት መርሐ ግብር ጋር በተያያዘ ባለን ግንዛቤ ላይ የተደረገውን ማስተካከያ ይዟል። ይህ የትምህርት መርሐ ግብር የሚከናወነው መቼ እንደሆነና በሥራው የሚካፈሉት እነማን እንደሆኑ እንመለከታለን። በተጨማሪም ይህ የትምህርት መርሐ ግብር በምድር ላይ ያሉ ሰዎችን በክርስቶስ ሺህ ዓመት ግዛት መጨረሻ ለሚኖረው ፈተና የሚያዘጋጃቸው እንዴት እንደሆነ እንመረምራለን።
-
-
“የጽድቅን ጎዳና እንዲከተሉ ብዙ ሰዎችን” መርዳትመጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022 | መስከረም
-
-
c ይህ ማብራሪያ የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል! በተባለው መጽሐፍ ምዕራፍ 17 እና በሐምሌ 1, 1987 መጠበቂያ ግንብ (እንግሊዝኛ) ከገጽ 21-25 ላይ የወጣውን ትምህርት የሚያስተካክል ነው።
d በአንጻሩ ግን በሐዋርያት ሥራ 24:15 ላይ ያሉት “ጻድቃን” እና “ጻድቃን ያልሆኑ ሰዎች” የሚሉት ቃላት እንዲሁም ዮሐንስ 5:29 ላይ ያሉት “መልካም የሠሩ” እና “ክፉ የሠሩ” የሚሉት አገላለጾች የሚያተኩሩት ትንሣኤ የሚያገኙ ሰዎች ከመሞታቸው በፊት ባከናወኑት ነገር ላይ ነው።
-