-
የአምላክ መንግሥት ተቋቁሟል!መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2022 | ሐምሌ
-
-
10. (ሀ) የዳንኤል ትንቢት የአንግሎ አሜሪካን ጥምረት በትክክል ገልጾታል የምንለው ለምንድን ነው? (ለ) ከየትኛው አደጋ መጠንቀቅ ይኖርብናል? (“ከሸክላው ተጠንቀቁ” የሚለውን ሣጥን ተመልከት።)
10 በመጀመሪያ፣ በራእዩ ላይ ከተጠቀሱት ከሌሎቹ የዓለም ኃያል መንግሥታት በተለየ መልኩ የአንግሎ አሜሪካ የዓለም ኃያል መንግሥት የተወከለው እንደ ወርቅ ወይም ብር ባለ ንጹሕ ንጥረ ነገር ሳይሆን በብረትና በሸክላ ቅልቅል ነው። ሸክላው ‘የሰውን ዘር’ ማለትም ተራውን ሕዝብ ያመለክታል። (ዳን. 2:43 ግርጌ) በዛሬው ጊዜ በግልጽ እንደሚታየው ሕዝቡ በምርጫ፣ በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እንቅስቃሴ፣ በተቃውሞ ሰልፍ እንዲሁም በሠራተኞች ማኅበራት አማካኝነት የሚያሳድረው ተጽዕኖ ይህ የዓለም ኃያል መንግሥት ፖሊሲዎቹን ለማስፈጸም ያለውን ኃይል ያዳክመዋል።
-