-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 28—ሆሴዕ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
4 ይህ የትንቢት መጽሐፍ በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ በርካታ ጊዜ መጠቀሱ የትንቢቱን እውነተኝነት ያረጋግጣል። ኢየሱስ ራሱ በኢየሩሳሌም ላይ ስለሚፈጸመው ፍርድ ሲናገር ሆሴዕ 10:8ን በመጥቀስ “በዚያን ጊዜም፣ ተራሮችን፣ ‘ውደቁብን’ ኰረብቶችንም፣ ‘ሰውሩን’ ይላሉ” ብሎ ተናግሯል። (ሉቃስ 23:30) ይኸው ጥቅስ በራእይ 6:16 ላይ በከፊል ተጠቅሶ ይገኛል። ማቴዎስ “ልጄን ከግብፅ ጠራሁት” የሚለው ትንቢት ፍጻሜውን እንዳገኘ ለመግለጽ ሆሴዕ 11:1ን ጠቅሷል። (ማቴ. 2:15) ይሁዳ በምርኮ ከመወሰዷ በፊት ከአሥሩ ነገድ መንግሥት መካከል ብዙ ሰዎች ወደ እርሷ በመሄዳቸውና ልጆቻቸውም ከምርኮ ከተመለሱት ሰዎች መካከል በመገኘታቸው ሆሴዕ መላው የእስራኤል ሕዝብ እንደገና ስለ መቋቋሙ የተናገረው ትንቢት ፍጻሜውን አግኝቷል። (ሆሴዕ 1:11፤ 2 ዜና 11:13-17፤ 30:6-12, 18, 25፤ ዕዝራ 2:70) መጽሐፉ ከዕዝራ ዘመን አንስቶ ‘እግዚአብሔር በሆሴዕ አማካኝነት የተናገረው ቃል’ መሆኑ ታምኖበት በዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች መካከል ትክክለኛ ቦታውን ይዟል።—ሆሴዕ 1:2
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 28—ሆሴዕ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
14 የሆሴዕ መጽሐፍ ይሖዋ በመንፈሱ አማካኝነት ባስነገራቸው ትንቢቶች ላይ ያለንን እምነት ያጠነክርልናል። ሆሴዕ እስራኤልንና ይሁዳን በተመለከተ የተናገረው ትንቢት በሙሉ ተፈጽሟል። እስራኤል ፍቅረኞቿ የነበሩት ጣዖት አምላኪ የሆኑት አጎራባች ብሔራት የተዉአት ከመሆኑም በላይ በ740 ከክርስቶስ ልደት በፊት በአሦር አማካኝነት የጥፋትን አውሎ ነፋስ አጭዳለች። (ሆሴዕ 8:7-10፤ 2 ነገ. 15:20፤ 17:3-6, 18) ይሁን እንጂ ሆሴዕ፣ ይሖዋ ለይሁዳ ምሕረት እንደሚያሳያትና በወታደራዊ ኃይል ባይሆንም እንኳ እንደሚያድናት አስቀድሞ ተናግሮ ነበር። ይህም በኢየሩሳሌም ላይ ስጋት ፈጥረው የነበሩትን 185,000 አሦራውያን የይሖዋ መልአክ በገደለበት ጊዜ ፍጻሜውን አግኝቷል። (ሆሴዕ 1:7፤ 2 ነገ. 19:34, 35) ያም ቢሆን ግን በሆሴዕ 8:14 ላይ የተነገረው “እኔ ግን በከተሞቻቸው ላይ እሳትን እለቃለሁ፤ ምሽጎቻቸውንም ይበላል” የሚለው ፍርድ ይሁዳንም ይጨምር ነበር፤ በመሆኑም ናቡከደነፆር ከ609-607 ከክርስቶስ ልደት በፊት ባለው ጊዜ ይሁዳንና ኢየሩሳሌምን ባድማ ባደረገበት ወቅት ይህ ትንቢት አሰቃቂ በሆነ መንገድ ፍጻሜውን አግኝቷል። (ኤር. 34:6, 7፤ 2 ዜና 36:19) ሆሴዕ እንደገና ስለመቋቋም የተናገራቸው በርካታ ትንቢቶች ይሖዋ ይሁዳንና እስራኤልን አንድ ላይ በሰበሰበበትና በ537 ከክርስቶስ ልደት በፊት በምርኮ ከነበሩበት ምድር ‘ተመልሰው በመጡበት’ ጊዜ ፍጻሜያቸውን አግኝተዋል።—ሆሴዕ 1:10, 11፤ 2:14-23፤ 3:5፤ 11:8-11፤ 13:14፤ 14:1-9፤ ዕዝራ 2:1፤ 3:1-3
-