-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 31—አብድዩ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
5 አብድዩ በኤዶም ላይ የተናገረው ትንቢት ሙሉ በሙሉ ተፈጽሟል! ትንቢቱ በስተ መጨረሻው ላይ እንዲህ ይላል:- “‘የዔሳው ቤት ገለባ ይሆናል፤ ያቃጥሉታል፤ ይበሉትማል፤ ከዔሳው ቤት የሚተርፍ፣ አይኖርም’ እግዚአብሔር ተናግሮአል።” (ቁጥር 18) ኤዶም የኖረው በሰይፍ ኃይል ነበር፣ በዚያው በሰይፍ ጠፍቷል፤ ዘሮቹም ድምጥማጣቸው ጠፍቷል። ስለዚህ የአብድዩ መጽሐፍ እውነተኛና ትክክለኛ መሆኑ ተረጋግጧል። አብድዩ የእውነተኛ ነቢይ መታወቂያ የሆኑት ማረጋገጫዎች በሙሉ አሉት:- ትንቢቱን የተናገረው በይሖዋ ስም ነው፣ የተናገረው ትንቢት ይሖዋን አስከብሯል እንዲሁም በታሪክ እንደተረጋገጠው ትንቢቱ በትክክል ተፈጽሟል። የስሙ ትርጉም “የይሖዋ አገልጋይ” መሆኑ ተገቢ ነው።
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 31—አብድዩ“ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
-
-
12 ጆሴፈስ እንደዘገበው በሁለተኛው መቶ ዘመን ከክርስቶስ ልደት በፊት ቀዳማዊ ጆን ሂርካነስ የተባለው የአይሁድ ንጉሥ የቀሩትን ኤዶማውያን ድል አድርጎ ከተቆጣጠራቸው በኋላ በግድ እንዲገረዙ አደረገ፤ ውሎ አድሮም በአይሁዳውያን ግዛት ተዋጡና በአይሁዳዊ ገዢ ይተዳደሩ ጀመር። ሮማውያን ኢየሩሳሌምን በ70 ከክርስቶስ ልደት በኋላ ሲያጠፏት የኤዶማውያን ስም ከታሪክ ገጾች ፈጽሞ ተደመሰሰ።c አብድዩ “ለዘላለምም ትጠፋለህ . . . ከዔሳው ቤት የሚተርፍ፣ አይኖርም” በማለት የተናገረው ትንቢት በትክክል ተፈጽሞባቸዋል።—አብ. 10, 18
-