-
ምሕረት ስለ ማሳየት ትምህርት አግኝቷልመጠበቂያ ግንብ—2009 | ሚያዝያ 1
-
-
ንጉሡም ቢሆን አምላካዊ ፍርሃት አደረበት። ከዙፋኑ ወረደ፤ ልብሰ መንግሥቱንም አወለቀ፤ እንደ ሕዝቡ ማቅ ለብሶ “በዐመድ ላይ ተቀመጠ።” ንጉሡ “ከመሳፍንቱ” ጋር በመተባበር፣ ሕዝቡ የጀመረው ጾም በመንግሥት ደረጃ እንዲፈጸም የሚደነግግ አዋጅ አወጣ። ሕዝቡ ሁሉ፣ ሌላው ቀርቶ የቤት እንሳሳትም እንኳ ማቅ እንዲለብሱ አዘዘ።c ሕዝቡ በክፋታቸውና በዓመፃቸው በደለኞች መሆናቸውን በትሕትና አምኖ ተቀበለ። ከዚህም በላይ ንጉሡ ‘እኛ እንዳንጠፋ አምላክ ከጽኑ ቍጣው ይመለስ እንደ ሆነ ማን ያውቃል?’ በማለት እውነተኛው አምላክ ንስሐ መግባታቸውን ሲመለከት ሊራራላቸው እንደሚችል ያለውን ተስፋ ገለጸ።—ዮናስ 3:6-9
-
-
ምሕረት ስለ ማሳየት ትምህርት አግኝቷልመጠበቂያ ግንብ—2009 | ሚያዝያ 1
-
-
c ንጉሡ የወሰደው እንዲህ ያለው እርምጃ ያልተለመደ ነገር ሊመስል ቢችልም ከዚያ በፊት ተደርጎ የማያውቅ ነገር አይደለም። ግሪካዊው የታሪክ ምሑር ሄሮዶተስ፣ የጥንቶቹ ፋርሳውያን አንድ ተወዳጅ ጄኔራል በሞተ ጊዜ በሐዘን ሥነ ሥርዓቱ ላይ ከብቶቻቸውም እንዲካፈሉ እንዳደረጉ ገልጿል።
-