-
ሌሎችን በይሖዋ ዓይን ለማየት ጣሩመጠበቂያ ግንብ—2003 | መጋቢት 15
-
-
5. ዮናስ የተሰጠው ተልእኮ ምን ነበር? እርሱስ ምን አደረገ?
5 በዮአስ ልጅ በዳግማዊ ኢዮርብዓም የግዛት ዘመን ዮናስ በሰሜናዊው የእስራኤል መንግሥት ነቢይ ሆኖ አገልግሏል። (2 ነገሥት 14:23-25) በአንድ ወቅት ይሖዋ ዮናስን የኃያልዋ አሦር ግዛት ዋና ከተማ ወደ ነበረችው ወደ ነነዌ እንዲሄድ አዘዘው። ወደዚያ እንዲሄድ የታዘዘው ለምን ነበር? ታላቅዋ ከተማ ጥፋት እንደተፈረደባት ነዋሪዎቹን ለማስጠንቀቅ ነበር። (ዮናስ 1:1, 2) ዮናስ የአምላክን መመሪያ ከመታዘዝ ይልቅ ወደሌላ ቦታ ሸሽቶ ሄደ! በመርከብ ተሳፍሮ ከነነዌ በጣም ርቃ ወደምትገኘው ወደ ተርሴስ ኮበለለ።—ዮናስ 1:3
-
-
ሌሎችን በይሖዋ ዓይን ለማየት ጣሩመጠበቂያ ግንብ—2003 | መጋቢት 15
-
-
9. መንገደኞቹን ከባድ ማዕበል ባስጨነቃቸው ወቅት የትኞቹ የዮናስ ባሕርያት በግልጽ ታይተዋል?
9 ዮናስ ይሖዋ ወዳዘዘው አካባቢ ለመሄድ ፈቃደኛ ስላልነበረ መርከብ ተሳፍሮ ወደ ሌላ አቅጣጫ ለመጓዝ ተነሳ። ይሁን እንጂ ይሖዋ በእርሱ ተስፋ አልቆረጠም ወይም ሌላ ሰው እንዲተካው አላደረገም። ከዚህ ይልቅ ዮናስ የተልእኮውን አስፈላጊነት እንዲገነዘብ ሊረዳው ፈለገ። አምላክ ባሕሩ ላይ ከባድ ማዕበል እንዲነሳ ሲያደርግ ዮናስ የተሳፈረባት መርከብ በሞገዱ ትናወጥ ጀመር። በዮናስ ምክንያት ንጹሐን ሰዎች ጥፋት ሊደርስባቸው ነበር! (ዮናስ 1:4) ዮናስ ምን እርምጃ ይወስድ ይሆን? በእርሱ ምክንያት ተሳፋሪዎቹ እንዲሞቱ ስላልፈለገ “አንሥታችሁ ወደ ባሕር ጣሉኝ፣ ባሕሩም ጸጥ ይልላችኋል” አላቸው። (ዮናስ 1:12) በዚህ ጊዜ ዮናስን ወደ ባሕሩ የጣሉት ሲሆን እርሱም ይሖዋ ያድነኛል የሚል ግምት አልነበረውም። (ዮናስ 1:15) የሆነ ሆኖ መንገደኞቹ ከጥፋት እንዲድኑ ሲል ሕይወቱን ለመስጠት ፈቃደኛ ነበር። ዮናስ የወሰደው ይህ እርምጃ ደፋር፣ ትሑትና አፍቃሪ መሆኑን አያሳይም?
-