-
‘እጆቻችሁ አይዛሉ’መጠበቂያ ግንብ—1996 | መጋቢት 1
-
-
16. አብዛኞቹ የሕዝበ ክርስትና አብያተ ክርስቲያናት አባላት ምን አስተሳሰብ አላቸው? ሆኖም ይሖዋ ምን ማበረታቻ ይሰጠናል?
16 በዛሬው ጊዜ ግድ የለሽነት በብዙ የምድር ክፍሎች በተለይም በበለጸጉት አገሮች ውስጥ በእጅጉ ተስፋፍቷል። ሌላው ቀርቶ የሕዝበ ክርስትና አብያተ ክርስቲያናት አባላት እንኳ ይሖዋ አምላክ በአሁኑ ጊዜ በሰዎች ጉዳይ እጁን ያስገባል ብለው አያምኑም። እነዚህ ሰዎች በማፌዝ ወይም “አልፈልግም” የሚል አጭር መልስ በመስጠት የመንግሥቱን ምሥራች ለማድረስ የምናደርገውን ጥረት መና ለማስቀረት ይሞክራሉ። እነዚህ ሁኔታዎች እያሉ በምስክርነቱ ሥራ መጽናት ተፈታታኝ ሊሆን ይችላል። ያለንን ጽናት ይፈትነዋል። ሆኖም ይሖዋ በሶፎንያስ ትንቢት አማካኝነት እንደሚከተለው በማለት ታማኝ ሕዝቦቹን ያበረታታል፦ “እጆችሽም አይዛሉ። አምላክሽ ይሖዋ በመካከልሽ ነው። እርሱ ኃያል እንደመሆኑ መጠን ይታደጋል። በደስታ በአንቺ ደስ ይለዋል፣ በፍቅሩም ያርፋል፣ በእልልታም በአንቺ ደስ ይለዋል።”—ሶፎንያስ 3:16, 17 አዓት
17. አዳዲስ የሆኑ የሌሎች በጎች አባላት ሊከተሉት የሚገባቸው ግሩም ምሳሌ ምንድን ነው? እንዴትስ?
17 ዘመናዊው የይሖዋ ሕዝቦች ታሪክ እንደሚያሳየው ቅቡዓኑና ረጅም ዕድሜ ያሳለፉ የሌሎች በጎች አባላት በእነዚህ የመጨረሻ ቀኖች ውስጥ አስደናቂ የመሰብሰብ ሥራ አከናውነዋል። እነዚህ ታማኝ ክርስቲያኖች ለአያሌ አሥርተ ዓመታት ጸንተዋል። በሕዝበ ክርስትና ሥር ያሉ አብዛኞቹ ሰዎች የሚያሳዩአቸው ግድ የለሽነት ተስፋ እንዲያስቆርጣቸው አልፈቀዱም። ከሌሎች በጎች መካከል የሆኑ አዳዲስ ሰዎችም ቢሆኑ በዛሬው ጊዜ በብዙ አገሮች በተስፋፋው ሰዎች ለመንፈሳዊ ነገሮች በሚያሳዩት ግድ የለሽነት ተስፋ መቁረጥ የለባቸውም። ‘እጆቻቸው ሊዝሉ’ ወይም ሊታክቱ አይገባም። መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! መጽሔቶችን እንዲሁም በግ መሰል ሰዎችን ስለ ይሖዋ ቀንና ከዚያ በኋላ ስለሚመጡ በረከቶች እውነተኛውን እውቀት እንዲያገኙ ለመርዳት የተዘጋጁ ሌሎች ጽሑፎችን ለማበርከት እያንዳንዱን አጋጣሚ መጠቀም ይገባቸዋል።
-
-
‘እጆቻችሁ አይዛሉ’መጠበቂያ ግንብ—1996 | መጋቢት 1
-
-
18, 19. (ሀ) በማቴዎስ 24:13 እና በኢሳይያስ 35:3, 4 ላይ ለመጽናት የሚያስችል ምን ማበረታቻ ተሰጥቷል? (ለ) በይሖዋ አገልግሎት በአንድነት ወደ ፊት ከገፋን የምንባረከው እንዴት ነው?
18 ኢየሱስ “እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል” ብሏል። (ማቴዎስ 24:13) ስለዚህ ታላቁን የይሖዋ ቀን ስንጠብቅ ‘እጆቻችን ሊደክሙ’ ወይም ‘ጉልበቶቻችን ሊላሉ’ አይገባም! (ኢሳይያስ 35:3, 4) የሶፎንያስ ትንቢት ስለ ይሖዋ ሲናገር “ኃያል እንደመሆኑ መጠን ይታደጋል” በማለት ያረጋግጥልናል። (ሶፎንያስ 3:17 አዓት) አዎን፣ ይሖዋ በሕዝቦቹ ላይ ‘የታበዩትን’ የፖለቲካ መንግሥታት እንዲያደቃቸው ለልጁ ትእዛዝ በመስጠት “እጅግ ብዙ ሰዎች” ‘የታላቁን መከራ’ የመጨረሻ ምዕራፍ በሕይወት እንዲያልፉ ያደርጋል።—ራእይ 7:9, 14፤ ሶፎንያስ 2:10, 11፤ መዝሙር 2:7-9
-