-
“በጉጉት እየተጠባበቃችሁኝ ኑሩ”መጠበቂያ ግንብ—1996 | መጋቢት 1
-
-
13. ሶፎንያስ በሞዓብ፣ በአሞንና በአሦር ላይ የተናገረው የፍርድ መልእክት ምንድን ነው?
13 በተጨማሪም ይሖዋ ሕዝቡን ባሠቃዩት ብሔራት ላይ ያለውን ቁጣ በነቢዩ ሶፎንያስ አማካኝነት ተናግሯል። እንዲህ ብሏል፦ “በሕዝቤም ላይ ያላገጡባትን፣ በድንበራቸውም ላይ እየታበዩ የተናገሩባትን የሞዓብን ማላገጥና የአሞንን ልጆች ስድብ ሰምቻለሁ። ስለዚህ የእስራኤል አምላክ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እኔ ሕያው ነኝና በእርግጥ ሞዓብ እንደ ሰዶም፣ የአሞንም ልጆች እንደ ገሞራ፣ የሳማ ስፍራና የጨው ጉድጓድ ለዘላለምም ምድረ በዳ ሆነው ይኖራሉ፤ . . . እርሱም በሰሜን ላይ እጁን ይዘረጋል፣ አሦርንም ያጠፋል፤ ነነዌንም ባድማ፣ እንደ በረሃም ደረቅ ያደርጋታል።”—ሶፎንያስ 2:8, 9, 13
14. የውጪ ብሔራት በእስራኤላውያንና በአምላካቸው በይሖዋ ላይ ‘እንደታበዩ’ የሚያሳይ ምን ማስረጃ አለ?
14 ሞዓብና አሞን የእስራኤላውያን የረጅም ጊዜ ጠላቶች ነበሩ። (ከመሳፍንት 3:12-14 ጋር አወዳድር።) ፓሪስ ውስጥ በሉቭር ሙዚየም በሚገኘው የሞዓባውያን ጽላት ላይ የተቀረጸው ጽሑፍ የሞዓባውያን ንጉሥ የነበረው ሞሳ የተናገራቸውን የጉራ ቃላት ይዟል። ካሞሽ በተባለው አምላኩ እርዳታ ብዙ የእስራኤል ከተሞችን እንደያዘ በኩራት ይተርካል። (2 ነገሥት 1:1) አሞናውያን ሚልኮም በተባለው አምላካቸው ስም ጋድ ተብሎ የሚጠራውን የእስራኤል ክልል እንደያዙ በሶፎንያስ ዘመን ይኖር የነበረው ኤርምያስ ተናግሯል። (ኤርምያስ 49:1) በተጨማሪም የአሦራውያን ንጉሥ ስልምናሶር አምስተኛ ሶፎንያስ ከኖረበት ዘመን አንድ መቶ ዓመት ቀደም ብሎ ሰማርያን በመውረር በቁጥጥሩ ሥር አውሏት ነበር። (2 ነገሥት 17:1-6) ከጥቂት ጊዜ በኋላ ንጉሥ ሰናክሬም በይሁዳ ላይ ጥቃት በመሰንዘር በይሁዳ የሚገኙ አያሌ የተመሸጉ ከተሞች በቁጥጥሩ ሥር አድርጎ ነበር። አልፎ ተርፎም ኢየሩሳሌምን እንደሚወጋ ዝቶ ነበር። (ኢሳይያስ 36:1, 2) የአሦር ንጉሥ ቃል አቀባይ ኢየሩሳሌምን አሳልፈው እንዲሰጡ ሲጠይቅ በይሖዋ ላይ የትዕቢት ቃል ተናግሮ ነበር።—ኢሳይያስ 36:4-20
-
-
“በጉጉት እየተጠባበቃችሁኝ ኑሩ”መጠበቂያ ግንብ—1996 | መጋቢት 1
-
-
15. ይሖዋ በሕዝቦቹ ላይ የታበዩ ብሔራት የሚያመልኳቸውን አማልክት ያዋረደው እንዴት ነበር?
15 መዝሙር 83 “ኑ ከሕዝብ እናጥፋቸው፣ ደግሞም የእስራኤል ስም አይታሰብ” ብለው ጉራቸውን በመንዛት በእስራኤል ላይ የታበዩ እንደ ሞዓብ፣ አሞንና አሦር ያሉ ብዙ ብሔራት ይጠቅሳል። (መዝሙር 83:4) የሠራዊት ጌታ ይሖዋ እነዚህን ሁሉ ትዕቢተኛ ብሔራትና አማልክቶቻቸውን እንደሚያዋርድ ነቢዩ ሶፎንያስ በድፍረት አስታውቋል። “በሠራዊት ጌታ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ አላግጠዋልና፣ እየታበዩም ተናግረዋልና ይህ ስለ ትዕቢታቸው ያገኛቸዋል። እግዚአብሔር በእነርሱ ላይ የተፈራ ይሆናል፣ የምድርንም አማልክት ሁሉ ያከሳቸዋል፤ በአሕዛብም ደሴቶች ሁሉ ላይ የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ በስፍራቸው ሆነው ለእርሱ ይሰግዳሉ።”—ሶፎንያስ 2:10, 11
-
-
“በጉጉት እየተጠባበቃችሁኝ ኑሩ”መጠበቂያ ግንብ—1996 | መጋቢት 1
-
-
18. (ሀ) ኢየሩሳሌም መለኮታዊ ቅጣት የደረሰባት እንዴት ነበር? ለምንስ? (ለ) ሶፎንያስ ሞዓብንና አሞንን በተመለከተ የተናገረው ትንቢት የተፈጸመው እንዴት ነበር?
18 ይሖዋን በጉጉት ይጠባበቁ የነበሩ አያሌ አይሁዳውያን ይሖዋ በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ የወሰዳቸው የቅጣት እርምጃዎች ለማየት በቅተዋል። ሶፎንያስ ኢየሩሳሌምን በተመለከተ እንዲህ በማለት ተንብዮ ነበር፦ “ለዓመፀኛይቱና ለረከሰች ለአስጨናቂይቱም ከተማ ወዮላት! ድምፅን አልሰማችም፣ ተግሣጽንም አልተቀበለችም፤ በእግዚአብሔርም አልታመነችም፣ ወደ አምላክዋም አልቀረበችም።” (ሶፎንያስ 3:1, 2) ኢየሩሳሌም ታማኝ ሆና ባለመገኘቷ የተነሳ ሁለት ጊዜ በባቢሎናውያን ከመወረሯም በላይ በመጨረሻ በ607 ከዘአበ ጠፍታለች። (2 ዜና መዋዕል 36:5, 6, 11-21) የአይሁዳውያን ታሪክ ጸሐፊ የሆነው ጆሴፈስ እንደተናገረው ኢየሩሳሌም በጠፋች በአምስተኛው ዓመት ባቢሎናውያን በሞዓብና በአሞን ላይ ጦርነት ከፍተው ድል አድርገዋቸዋል። ከዚያም በተተነበየው መሠረት ሞዓባውያንና አሞናውያን ከምድረ ገጽ ጠፉ።
-