-
ሰው ሁሉ ይሖዋን ያክብር!መጠበቂያ ግንብ—1997 | ጥር 1
-
-
19. በሐጌ 2:6, 7 ፍጻሜ መካፈል የምንችለው እንዴት ነው?
19 በሐጌ 2:6, 7 ላይ ያለው ትንቢት ዘመናዊ ፍጻሜውን ሲያገኝ እኛም የዚሁ ተካፋይ መሆናችን አስደሳች መብት ነው:- “ገና አንድ ጊዜ በቅርብ ዘመን እኔ ሰማያትንና ምድርን ባሕርንና የብስንም አናውጣለሁ፤ አሕዛብንም አናውጣለሁ፣ በአሕዛብም የተመረጠው ሁሉ ዕቃ ይመጣል፤ ይህንም ቤት በክብር እሞላዋለሁ፣ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” በዚህ በ20ኛው መቶ ዘመን ዓለም ውስጥ ስግብግብነት፣ ሙስና እና ጥላቻ እንደ አሸን እየፈሉ ነው። በእውነትም ይህ ዓለም በመጨረሻ ቀኖቹ ላይ ነው፤ ይሖዋም ምሥክሮቹ ‘የበቀል ቀኑን እንዲያውጁ’ በመላክ ‘እያናወጠው’ ነው። (ኢሳይያስ 61:2) ይህ የመጀመሪያ ደረጃ ነውጥ ዛሬ ያለው ዓለም በአርማጌዶን ሲመደሰስ ታላቁ መደምደሚያው ላይ ይደርሳል፤ ይህ ጊዜ ከመድረሱ በፊት ግን ይሖዋ ‘በአሕዛብ ሁሉ የተመረጠውን ዕቃ’ ማለትም ገርና በግ መሰል የሆኑትን የምድር ሰዎች እንዲያገለግሉት ወደ እርሱ በመሳብ ላይ ነው። (ዮሐንስ 6:44) በአሁኑ ጊዜ እነዚህ “እጅግ ብዙ ሰዎች” በይሖዋ የአምልኮ ቤት ምድራዊ አደባባይ ውስጥ ‘ቅዱስ አገልግሎት ያቀርባሉ።’— ራእይ 7:9, 15
-
-
የይሖዋ ቤት ያገኘው ታላቅ ክብርመጠበቂያ ግንብ—1997 | ጥር 1
-
-
የይሖዋ ቤት ያገኘው ታላቅ ክብር
“ይህንም ቤት በክብር እሞላዋለሁ፣ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር [“ይሖዋ፣” አዓት]።”— ሐጌ 2:7
1. መንፈስ ቅዱስ ከእምነትና ከሥራ ጋር የሚዛመደው እንዴት ነው?
አንዲት የይሖዋ ምሥክር ከቤት ወደ ቤት ስትሰብክ የጰንጠቆስጤ ሃይማኖት ተከታይ የሆነች አንዲት ሴት ታገኛለች። ሴትየዋ ‘መንፈስ ቅዱስ የተሰጠን እኛ ነን፤ ሥራውን ግን የምትሠሩት እናንተ ናችሁ’ ስትል የተሰማትን ተናገረች። ከዚያም ምሥክሯ አንድ ሰው መንፈስ ቅዱስ ካለው የአምላክን ሥራ ለመሥራት እንደሚያነሳሳው በዘዴ አብራራችላት። ያዕቆብ 2:17 “ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው” ይላል። የይሖዋ መንፈስ ምሥክሮቹ ጠንካራ እምነት እንዲያዳብሩ ከመርዳቱም ሌላ የጽድቅ ሥራዎችን እንዲሠሩ በማድረግ ‘ቤቱን በክብር ሞልቶታል።’ ዋነኛው ሥራ ‘ለአሕዛብ ሁሉ ምሥክር እንዲሆን የመንግሥቱን ወንጌል በዓለም ሁሉ መስበክ’ ነው። ሥራው ይሖዋ የሚፈልገው ደረጃ ላይ ሲደርስ ‘ፍጻሜው ይመጣል።’— ማቴዎስ 24:14
-