-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
10. የይሖዋ ታማኝ ምሥክሮች በሚረገጡበት ጊዜ ምን ማድረግ ይገባቸው ነበር?
10 እነዚህ ታማኝ ክርስቲያኖች ቢረገጡም እንኳን የይሖዋ ታማኝ ምሥክሮች ከመሆን አላፈገፈጉም። በዚህም ምክንያት ትንቢቱ እንዲህ በማለት ይቀጥላል:- “ለሁለቱም ምስክሮቼ ማቅ ለብሰው ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን ትንቢት ሊናገሩ እሰጣለሁ። እነዚህ በምድር ጌታ ፊት የሚቆሙ ሁለቱ ወይራዎችና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው።”—ራእይ 11:3, 4
-
-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
13. (ሀ) ቅቡዓን ክርስቲያኖች በሁለት ምሥክሮች መመሰላቸው ምን ያመለክታል? (ለ) ዮሐንስ ሁለቱን ምሥክሮች “ሁለቱ የወይራ ዛፎችና ሁለቱ መቅረዞች” ብሎ መጥራቱ የትኛውን የዘካርያስ ትንቢት ያስታውሰናል?
13 በሁለት ምሥክሮች መመሰላቸው ራሱ መልእክታቸው የተረጋገጠና ትክክለኛ መሆኑን ያረጋግጥልናል። (ከዘዳግም 17:6ና ከዮሐንስ 8:17, 18 ጋር አወዳድር።) ዮሐንስ “በምድር ጌታ ፊት የሚቆሙ” “ሁለቱ የወይራ ዛፎችና ሁለቱ መቅረዞች” እንደሆኑ ተናግሮላቸዋል። ይህም ባለ ሰባት ቅርንጫፍ መቅረዝና ሁለት የወይራ ዛፎች የተመለከተውን የዘካርያስን ትንቢት የሚጠቅስ ይመስላል። የወይራ ዛፎቹ “በምድር ሁሉ ጌታ አጠገብ የቆሙት” “ሁለቱ የተቀቡ” ሰዎች ማለትም ገዥውን ዘሩባቤልና ሊቀ ካህኑን ኢያሱ እንደሚያመለክቱ ተነግሮአል።—ዘካርያስ 4:1-3, 14
14. (ሀ) ዘካርያስ በራእይ የተመለከታቸው ሁለት የወይራ ዛፎች የምን ምሳሌዎች ነበሩ? መቅረዙስ? (ለ) በአንደኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በቅቡዓን ክርስቲያኖች ላይ ምን ደርሶባቸዋል?
14 ዘካርያስ ይኖር የነበረበት ዘመን የእድሳትና የግንባታ ዘመን ነበር። የሁለቱን የወይራ ዛፎች ራእይ መመልከቱ ደግሞ ዘሩባቤልና ኢያሱ ሕዝቦቻቸውን ለሥራ በሚያነሳሱበት ጊዜ የይሖዋ መንፈስ አብሮአቸው እንደሚሆን የሚያመልክት ነው። ዘካርያስ በራእይ የተመለከተው የመቅረዝ ራእይ “የጥቂቱን ነገር ቀን” እንዳይንቅ የሚያሳስበው ነበር። ምክንያቱም የይሖዋ ዓላማ የሚፈጸመው “በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፣ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር [“ይሖዋ፣” NW]።” (ዘካርያስ 4:6, 10፤ 8:9) በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ለሰው ልጆች የእውነትን ብርሃን በትጋት ያደርሱ የነበሩት ጥቂት ክርስቲያኖችም በተመሳሳይ የግንባታ ሥራ ይፈጽማሉ። እነርሱም ለሌሎች የመጽናናት ምንጭ ይሆናሉ። ቁጥራቸው ጥቂት ቢሆንም “የጥቂቱን ነገር ቀን” ሳይንቁ በይሖዋ ኃይል መመካትን ይማራሉ።
-