የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ይሖዋ ሰላምንና እውነትን አትረፍርፎ ይሰጣል
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥር 1
    • ‘ለጽዮን እቀናለሁ’

      6, 7. ይሖዋ ‘ለጽዮን በታላቅ ቅንዓት የቀናው’ በምን በምን መንገዶች ነበር?

      6 እነዚህ ቃላት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጠቀሱት በዘካርያስ 8:2 ላይ ነው። እዚህ ጥቅስ ላይ “የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ስለ ጽዮን ታላቅ ቅንዓት ቀንቻለሁ፣ በታላቅም ቁጣ ስለ እርስዋ ቀንቻለሁ” የሚል እናነባለን። ይሖዋ ለሕዝቡ እቀናለሁ እንዲሁም ታላቅ ቅንዓት አለኝ በማለት ቃል መግባቱ ሰላማቸውን ለመመለስ ልዩ ትኩረት እንደሚያደርግ ያሳያል። እስራኤላውያን ወደ አገራቸው መመለሳቸውና ቤተ መቅደሱ እንደገና መሠራቱ ለዚህ ቅንዓቱ ማስረጃ ነበር።

      7 ታዲያ የይሖዋን ሕዝቦች ይቃወሙ የነበሩት ሰዎች ምን ሆኑ? ለሕዝቦቹ የነበረው ቅንዓት በእነዚህ ጠላቶች ላይ ካሳየው ‘ታላቅ ቁጣ’ ጋር የሚመጣጠን ነበር። ታማኝ አይሁዳውያን እንደገና በተሠራው ቤተ መቅደስ ውስጥ የአምልኮ ሥርዓት ሲፈጽሙ በወቅቱ ወድቃ የነበረችው የባቢሎን ኃያል መንግሥት በደረሰባት ዕጣ ላይ ሊያሰላስሉ ይችሉ ነበር። በተጨማሪም ቤተ መቅደሱ እንደገና እንዳይሠራ ለማድረግ ይጥሩ የነበሩት ጠላቶች ምን ያህል እንዳልተሳካላቸው ሊያስቡ ይችሉ ነበር። (ዕዝራ 4:1-6፤ 6:3) ከዚህም በላይ ይሖዋ የሰጠውን ተስፋ በመፈጸሙ ሊያመሰግኑት ይችሉ ነበር። ቅንዓቱ ድል እንዲቀዳጁ አብቅቷቸዋል!

  • ይሖዋ ሰላምንና እውነትን አትረፍርፎ ይሰጣል
    መጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥር 1
    • 9. “የአምላክ እስራኤል” በ1919 ምን አስደናቂ ለውጥ ተመልክቷል?

      9 እነዚህ ሁለት መግለጫዎች ለጥንቷ እስራኤል ትልቅ ትርጉም የነበራቸው ቢሆንም ይህ 20ኛው መቶ ዘመን ወደ ፍጻሜው በቀረበ መጠን ለእኛ የበለጠ ትርጉም ይኖራቸዋል። የጥንት እስራኤላውያን ወደ ባቢሎን ተማርከው እንደተወሰዱ ሁሉ ወደ 80 ከሚጠጉ ዓመታት በፊት በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ወቅት “የአምላክ እስራኤል”ን ይወክሉ የነበሩ በጥቂት ሺዎች የሚቆጠሩ ቅቡዓን በመንፈሳዊ ሁኔታ ተማርከው ነበር። (ገላትያ 6:16) በአንድ ትንቢታዊ መግለጫ ላይ በአደባባይ እንደ ተጣሉ ሬሳዎች ሆነው ተገልጸው ነበር። ሆኖም ይሖዋን “በመንፈስና በእውነት” ለማምለክ ልባዊ ፍላጎት ነበራቸው። (ዮሐንስ 4:24) ስለዚህ ይሖዋ በ1919 በመንፈሳዊ ሞተው ከነበሩበት ሁኔታ በማስነሣት ከምርኮ ነፃ አወጣቸው። (ራእይ 11:7-13) በዚህ መንገድ ይሖዋ “በውኑ አገር [“ምድር” አዓት] በአንድ ቀን ታምጣለችን? ወይስ በአንድ ጊዜ ሕዝብ ይወለዳልን?” ለሚለው የኢሳይያስ ትንቢታዊ ጥያቄ አዎን በማለት የሚያስተጋባ ምላሽ ሰጠ። (ኢሳይያስ 66:8) በ1919 የይሖዋ ሕዝቦች በራሳቸው “ምድር” ወይም በምድር ላይ ባላቸው መንፈሳዊ ርስት ውስጥ እንደገና እንደ አንድ መንፈሳዊ ብሔር ሆነው ተገኝተዋል።

      10. ቅቡዓን ክርስቲያኖች ከ1919 ጀምሮ በራሳቸው “ምድር” ውስጥ ያገኟቸው በረከቶች ምንድን ናቸው?

      10 ቅቡዓን ክርስቲያኖች በዚያ ምድር ያላንዳች ስጋት ተቀምጠው በታላቁ መንፈሳዊ ቤተ መቅደስ ውስጥ በማገልገል ላይ ናቸው። የኢየሱስን ምድራዊ ንብረቶች እንዲንከባከቡ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በመቀበላቸው “ታማኝና ልባም ባሪያ” እንዲሆኑ ተሹመዋል፤ 20ኛው መቶ ዘመን ወደ መደምደሚያው እየተቃረበ በሄደበት በዚህ ወቅትም እንኳን ይህን ኃላፊነት በመወጣት ላይ ናቸው። (ማቴዎስ 24:45-47) ይሖዋ ‘የሰላም አምላክ’ መሆኑን በሚገባ ተምረዋል።—1 ተሰሎንቄ 5:23

      11. የሕዝበ ክርስትና የሃይማኖት መሪዎች የአምላክ ሕዝብ ጠላቶች መሆናቸውን ያሳዩት እንዴት ነው?

      11 ታዲያ የአምላክ እስራኤል ጠላቶች ምን ይሆናሉ? ይሖዋ ለሕዝቡ ያለው ቅንዓት በጠላቶቹ ላይ ከሚያወርደው ቁጣ ጋር ይመጣጠናል። የሕዝበ ክርስትና የሃይማኖት መሪዎች በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ወቅት ይህን እውነትን የሚናገር አነስተኛ የክርስቲያኖች ቡድን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት አድርገው ሳይሳካላቸው ቀርቷል። የሕዝበ ክርስትና ቀሳውስት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በአንድ ነገር ሕብረት ፈጥረው ነበር፤ በጦርነቱ በሁለቱም ወገኖች የተሰለፉትን መንግሥታት የይሖዋ ምሥክሮችን እንዲያጠፏቸው ይገፋፏቸው ነበር። የሃይማኖት መሪዎች ዛሬም ቢሆን በብዙ አገሮች ውስጥ መንግሥታት የይሖዋ ምሥክሮችን ክርስቲያናዊ የስብከት ሥራ እንዲገድቡ ወይም እንዲያግዱ በማነሣሣት ላይ ይገኛሉ።

      12, 13. በሕዝበ ክርስትና ላይ የይሖዋ ቁጣ የተገለጠው እንዴት ነው?

      12 ይህን ጉዳይ ይሖዋ ሳይመለከተው አልቀረም። ሕዝበ ክርስትና ከመጀመሪያው የዓለም ጦርነት በኋላ ከቀሩት የታላቂቱ ባቢሎን ክፍሎች ጋር ወድቃለች። (ራእይ 14:8) ሕዝበ ክርስትና በመንፈሳዊ የሞተች መሆኗን በሕዝብ ፊት የሚያጋልጡና ወደፊት እንደምትጠፋ የሚያስጠነቅቁ ምሳሌያዊ የሆኑ ተከታታይ መቅሠፍቶች ከፈሰሱባት ከ1922 ጀምሮ ውድቀቷ በግልጽ ታይቷል። (ራእይ 8:7 እስከ 9:21) በመላው ዓለም ሚያዝያ 23, 1995 “የሐሰት ሃይማኖት ጥፋት ቀርቧል” በሚል ርዕስ ንግግር ከተሰጠ በኋላ በመቶ ሚልዮን በሚቆጠሩ ቅጂዎች አንድ ልዩ የመንግሥት ዜና መሰራጨቱ አሁንም እነዚህ መቅሠፍቶች መፍሰሳቸውን እንደ ቀጠሉ ያረጋግጣል።

      13 በአሁኑ ጊዜ ሕዝበ ክርስትና በአሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ ትገኛለች። በዚህ በ20ኛው መቶ ዘመን በሙሉ በቀሳውስቶቿና በአገልጋዮቿ ቡራኬ በተቀበሉ አረመኔያዊ ጦርነቶች አባላቶቿ እርስ በርሳቸው ተጨፋጭፈዋል። በአንዳንድ አገሮች ውስጥ ሕዝበ ክርስትና ጨርሶ ተደማጭነት እያጣች መጥታለች። ሕዝበ ክርስትና ከቀሩት የታላቂቱ ባቢሎን ክፍሎች ጋር እንድትጠፋ ተወስኗል።—ራእይ 18:21

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ