-
ይሖዋ ሰላምንና እውነትን አትረፍርፎ ይሰጣልመጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥር 1
-
-
ሰላም ለይሖዋ ሕዝብ
14. ሰላም ያለውን አንድ ሕዝብ በተመለከተ የተሰጠው ትንቢታዊ መግለጫ ምንድን ነው?
14 በሌላ በኩል ግን ይሖዋ በተናገረው ሦስተኛ መግለጫ ላይ እንደ ተገለጸው በዚህ በ1996 ዓመት የይሖዋ ሕዝቦች ተመልሶ በተቋቋመው ምድራቸው ውስጥ የተትረፈረፈ ሰላም ያገኛሉ፤ መግለጫው እንዲህ ይላል፦ “የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ዳግመኛ ሽማግሌዎችና ባልቴቶች [“አሮጊቶች” አዓት] በኢየሩሳሌም አደባባይ ይቀመጣሉ፤ ሰውም ሁሉ ከዕድሜው ብዛት የተነሣ ምርኩዝ በእጁ ይይዛል። የከተማይቱም አደባባዮች በእነዚያ በሚጫወቱ ወንዶችና ሴቶች ልጆች ይሞላሉ።”—ዘካርያስ 8:4, 5
15. በብሔራት መካከል ጦርነቶች ቢኖሩም የአምላክ አገልጋዮች ምን ዓይነት ሰላም አግኝተዋል?
15 ይህ አስደሳች መግለጫ በዚህ በጦርነት በሚታመስ ዓለም ውስጥ አንድ አስደናቂ የሆነ ነገር ማለትም ሰላም ያላቸውን ሕዝቦች ይገልጻል። ከ1919 ጀምሮ “በሩቅም በቅርብም ላለው ሰላም ሰላም ይሁን፣ እፈውሰውማለሁ፣ ይላል እግዚአብሔር። ክፉዎች ግን . . . ሰላም የላቸውም ይላል አምላኬ” የሚሉት የኢሳይያስ ቃላት ፍጻሜያቸውን አግኝተዋል። (ኢሳይያስ 57:19-21) እርግጥ የይሖዋ ሕዝቦች የዓለም ክፍል ባይሆኑም ብሔራት በሚያደርጉት ሽኩቻ መነካታቸው አይቀርም። (ዮሐንስ 17:15, 16) በአንዳንድ አገሮች ውስጥ ከባድ ችግሮች ያጋጠማቸው ሲሆን እንዲያውም አንዳንዶቹ ተገድለዋል። ሆኖም እውነተኛ ክርስቲያኖች በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ሰላም አላቸው። በመጀመሪያ ደረጃ “በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላም” አግኝተዋል። (ሮሜ 5:1) በሁለተኛ ደረጃ እርስ በርሳቸው ሰላም አላቸው። “በመጀመሪያ ንጽሕት፣ በኋላም ሰላማዊ” የሆነችውን “ላይኛይቱን ጥበብ” ኮትኩተዋል። (ያዕቆብ 3:17 አዓት፤ ገላትያ 5:22-24) ከዚህም በላይ ወደፊት ይበልጥ በተሟላ መልኩ ሰላም የሚያገኙበትን ጊዜ በጉጉት ይጠባበቃሉ፤ በዚያን ጊዜ “ገሮች ምድርን ይወርሳሉ፣ በብዙም ሰላም ደስ ይላቸዋል።”—መዝሙር 37:11
-
-
ይሖዋ ሰላምንና እውነትን አትረፍርፎ ይሰጣልመጠበቂያ ግንብ—1996 | ጥር 1
-
-
17 በአሁኑ ጊዜ ‘አደባባዮቿ በወንዶችና በሴቶች ልጆች’ ማለትም የወጣትነት ብርታት በሚታይባቸው የይሖዋ ምሥክሮች ተሞልተዋል። በ1995 የአገልግሎት ዓመት 232 አገሮችና ደሴቶች ሪፖርት አድርገዋል። ይሁን እንጂ በቅቡዓንና በሌሎች በጎች መካከል ዓለም አቀፍ ፉክክር፣ የጎሣ ጥላቻና ተገቢ ያልሆነ ቅናት አይታይም። ሁሉም በፍቅር ተሳስረው መንፈሳዊ እድገት አሳይተዋል። በእርግጥም ዓለም አቀፉ የይሖዋ ምሥክሮች የወንድማማች ማኅበር በዓለም ውስጥ በዓይነቱ ብቸኛና ልዩ ነው።—ቆላስይስ 3:14፤ 1 ጴጥሮስ 2:17
-