የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 39—ሚልክያስ
    “ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
    • 4 የሚልክያስን መጽሐፍ ትክክለኛነት በተመለከተ በአይሁዳውያን ዘንድ ጥያቄ ተነስቶ አያውቅም። በክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ውስጥ ከሚልክያስ መጽሐፍ ላይ የተወሰዱ ጥቅሶች የሚገኙ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የትንቢቱን ፍጻሜ የሚያሳዩ በርካታ ሐሳቦች እናገኛለን። ይህም የሚልክያስ መጽሐፍ በአምላክ መንፈስ አነሳሽነት እንደተጻፈና በክርስቲያን ጉባኤ ዘንድ ተቀባይነት ያገኙት የዕብራይስጥ ቅዱሳን መጻሕፍት ክፍል እንደሆነ ያረጋግጣል።—ሚል. 1:2, 3—ሮሜ 9:13፤ ሚል. 3:1—ማቴ. 11:10 እንዲሁም ሉቃስ 1:76 እና 7:27፤ ሚል. 4:5, 6—ማቴ. 11:14 እና 17:10-13 እንዲሁም ማር. 9:11-13 እና ሉቃስ 1:17

  • የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ ቁጥር 39—ሚልክያስ
    “ቅዱሳት መጻሕፍት ሁሉ” ትክክለኛና ጠቃሚ ናቸው፣ ጥራዝ 15
    • 15 ከዚህም በላይ በሚልክያስ 4:5, 6 ላይ ይሖዋ “እነሆ፤ . . . ነቢዩ ኤልያስን እልክላችኋለሁ” ሲል ቃል ገብቶ ነበር። ይህ “ኤልያስ” ማን ነው? ኢየሱስም ሆነ ለዘካርያስ የተገለጠለት መልአክ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ሲናገሩ በዚህ ስም የተጠቀሙ ሲሆን ‘ሁሉንም ነገር የሚያስተካክለው’ እንዲሁም ‘ለጌታ የተገባ ሕዝብ የሚያዘጋጀው’ እርሱ መሆኑን ገልጸዋል። ይሁን እንጂ ሚልክያስ “ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ከመምጣቱ በፊት ነቢዩ ኤልያስ” እንደሚመጣ ስለገለጸ ስለ ኤልያስ የተነገረው ትንቢት በታላቁ መከራ ወቅትም ተጨማሪ ፍጻሜ ይኖረዋል።—ማቴ. 17:11፤ ሉቃስ 1:17፤ ማቴ. 11:14፤ ማር. 9:12

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ