-
ይሖዋ የክህደትን ጎዳና ይጠላልመጠበቂያ ግንብ—2002 | ግንቦት 1
-
-
5, 6. (ሀ) በተለይ ካህናቱ ተነቃፊ የሆኑት ለምን ነበር? (ለ) ይሖዋ ለካህናቱ ያለውን ንቀት የገለጸው እንዴት ነው?
5 በተለይ ካህናቱ ተነቃፊ ሆነው የተገኙት ለምንድን ነው? ሚል 2 ቁጥር 7 አንድ ግልጽ ምክንያት ይጠቁመናል:- “ካህኑ የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔር መልእክተኛ ነውና ከንፈሮቹ እውቀትን ይጠብቁ ዘንድ ይገባቸዋል፣ ሰዎችም ሕግን ከአፉ ይፈልጉ ዘንድ ይገባቸዋል።” አንድ ሺህ ከሚበልጡ ዓመታት ቀደም ብሎ በሙሴ በኩል ለእስራኤላውያን የተሰጠው የአምላክ ሕግ ካህናት ‘እግዚአብሔር የነገራቸውን ሥርዓት ሁሉ ለእስራኤል ልጆች የማስተማር’ ኃላፊነት እንዳለባቸው ይናገራል። (ዘሌዋውያን 10:11) የሚያሳዝነው ግን በአንድ ሌላ ወቅት ላይ የ2 ዜና መዋዕል 15:3 ጸሐፊ “እስራኤልም ብዙ ዘመን ያለ እውነተኛ አምላክ፣ ያለ አስተማሪም ካህን፣ ያለ ሕግም ይኖሩ ነበር” በማለት ዘግቧል።
6 በሚልክያስ ዘመን ይኸውም በአምስተኛው መቶ ዘመን ከዘአበ ካህናቱ የሚገኙበት ሁኔታ ከዚህ ጋር ተመሳሳይ ነበር። የአምላክን ሕግ ለሕዝቡ ማስተማራቸውን አቁመው ነበር። ስለዚህ እነዚያ ካህናት በአምላክ ፊት መጠየቃቸው የተገባ ነው። ይሖዋ በእነርሱ ላይ የተናገራቸውን ተግሣጽ ያዘሉ ቃላት ልብ በል። ሚልክያስ 2:3 “የመሥዋዕታችሁንም ፋንድያ በፊታችሁ ላይ እበትናለሁ” በማለት ይገልጻል። እንዴት ያለ ዘለፋ ነው! ለመሥዋዕት የሚቀርቡ እንስሳት ፈርስ ከሠፈር ውጪ ተወስዶ እንደሚቃጠል የሚታወስ ነው። (ዘሌዋውያን 16:27) ሆኖም ይሖዋ ፈርሱን በፊታቸው ላይ እንደሚበትን መናገሩ የሚያቀርቡለትን መሥዋዕትም ሆነ መሥዋዕቱን ያቀርቡ የነበሩትን ሰዎች በንቀት ዓይን እንደሚመለከታቸውና እንደማይቀበላቸው በግልጽ የሚያሳይ ነው።
-
-
ይሖዋ የክህደትን ጎዳና ይጠላልመጠበቂያ ግንብ—2002 | ግንቦት 1
-
-
11. በተለይ ጥንቃቄ ማድረግ የሚኖርባቸው እነማን ናቸው?
11 በዛሬው ጊዜ በጉባኤ ውስጥ የማስተማር መብት የተሰጣቸውን ሰዎች በማስመልከት ሚልክያስ 2:7 ጥሩ ማስጠንቀቂያ ይዟል። ከንፈራቸው ‘እውቀትን ይጠብቁ ዘንድ ይገባቸዋል፣ ሰዎችም ከአፋቸው ሕግን ይፈልጉ ዘንድ ይገባቸዋል’ ይላል። ያዕቆብ 3:1 “የባሰውን ፍርድ” ይቀበላሉ ስለሚል በእነዚህ አስተማሪዎች ጫንቃ ላይ ከባድ ኃላፊነት ተጭኗል። በቅንነትና በግለት እንዲያስተምሩ የሚጠበቅባቸው ቢሆንም እንኳ ትምህርታቸው በሙሉ በተጻፈው የአምላክ ቃልና የይሖዋ ድርጅት አዘጋጅቶ በሚያቀርበው ትምህርት ላይ የተመሠረተ መሆን ይኖርበታል። በዚህ መንገድ ‘ሌሎችን ለማስተማር’ ብቁ ይሆናሉ። ስለዚህም “የእውነትን ቃል በቅንነት የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፣ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ” ተብለው ተመክረዋል።—2 ጢሞቴዎስ 2:2, 15
12. እንዲያስተምሩ መብት የተሰጣቸው ሰዎች ምን ዓይነት ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል?
12 ጥንቃቄ የማናደርግ ከሆነ በምናስተምርበት ጊዜ የግል አመለካከታችንንና አስተያየታችንን ጨምረን ለማስተማር እንፈተን ይሆናል። በተለይ የእርሱ ሐሳብ የይሖዋ ድርጅት ከሚያስተምረው ጋር በሚጋጭበት ጊዜ እንኳን ከልክ በላይ በራሱ የመተማመን ዝንባሌ ያለው ሰው ለዚህ አደጋ የተጋለጠ ነው። ይሁን እንጂ ሚልክያስ ምዕራፍ 2 የጉባኤው አስተማሪዎች በጎቹን ሊያሰናክል ከሚችለው ከራሳቸው አመለካከት ይልቅ ከአምላክ የሚያገኙትን እውቀት በጥብቅ እንዲከተሉ ልንጠብቅባቸው እንደምንችል ያሳያል። ኢየሱስ “በእኔም ከሚያምኑ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፣ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር” በማለት ተናግሯል።—ማቴዎስ 18:6
-