-
ኢየሱስ በመንግሥቱ ክብር ሲመጣመጠበቂያ ግንብ—1997 | ግንቦት 15
-
-
3, 4. (ሀ) ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ ከመለወጡ ከስድስት ቀን በፊት ምን ብሎ ነበር? (ለ) ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ በተለወጠበት ወቅት ምን እንደተከሰተ ግለጽ።
3 ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ ከመለወጡ ከስድስት ቀን በፊት ለተከታዮቹ “የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ ያን ጊዜም ለሁሉ እንደ ሥራው ያስረክበዋል” ሲል ነግሯቸው ነበር። እነዚህ ቃላት ፍጻሜያቸውን የሚያገኙት “በነገሮች ሥርዓት መደምደሚያ” ላይ ነው። በተጨማሪም ኢየሱስ “እውነት እላችኋለሁ፣ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ” ሲል ተናግሯል። (ማቴዎስ 16:27, 28፤ 24:3 NW፤ 25:31-34, 41፤ ዳንኤል 12:4) ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ የተለወጠው በእነዚህ ቃላት ፍጻሜ መሠረት ነው።
-
-
ኢየሱስ በመንግሥቱ ክብር ሲመጣመጠበቂያ ግንብ—1997 | ግንቦት 15
-
-
5. ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ መለወጡ በሐዋርያው ጴጥሮስ ላይ ምን ውጤት አስከትሏል?
5 ሐዋርያው ጴጥሮስ ቀደም ብሎ ኢየሱስን “ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ” ሲል ጠርቶታል። (ማቴዎስ 16:16) ይሖዋ ከሰማይ የተናገራቸው ቃላት የዚህን አባባል ትክክለኛነት ያረጋገጡ ሲሆን ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ ሲለወጥ የታየበት ራእይ ደግሞ ክርስቶስ በመንግሥታዊ ሥልጣንና ክብር እንደሚመጣና በመጨረሻም በሰው ልጆች ላይ እንደሚፈርድ የሚያመለክት ነበር። ኢየሱስ በተአምራዊ ሁኔታ ከተለወጠ 30 ከሚበልጡ ዓመታት በኋላ ጴጥሮስ እንዲህ ሲል ጽፏል:- “የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ሳንከተል የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና መምጣት አስታወቅናችሁ። ከገናናው ክብር:- በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና፤ እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን።”— 2 ጴጥሮስ 1:16-18፤ 1 ጴጥሮስ 4:17
-