-
የአምላክን ትንቢታዊ ቃል በትኩረት ተከታተልመጠበቂያ ግንብ—2000 | ሚያዝያ 1
-
-
5. የኢየሱስን ተአምራዊ ለውጥ በራስህ አባባል እንዴት ትገልጸዋለህ?
5 የኢየሱስ ተአምራዊ ለውጥ ትንቢታዊ ክንውን ነበር። ኢየሱስ እንዲህ ብሏል:- “የሰው ልጅ ከመላእክቱ ጋር በአባቱ ክብር ይመጣ ዘንድ አለውና፤ . . . እውነት እላችኋለሁ፣ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያዩ ድረስ እዚህ ከሚቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንድ አሉ።” (ማቴዎስ 16:27, 28) ታዲያ ከሐዋርያቱ መካከል ኢየሱስ በመንግሥቱ ሲመጣ የተመለከቱ ነበሩ? ማቴዎስ 17:1-7 እንዲህ ይላል:- “ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ።” እንዴት ያለ የሚያስገርም ክንውን ነው! “ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፣ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፣ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው።” እንዲሁም “ብሩህ ደመና ጋረዳቸው።” አምላክ ራሱም “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት” ብሎ ሲናገር ሰሙ። “ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር። ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና:- ተነሡ አትፍሩም አላቸው።”
-
-
የአምላክን ትንቢታዊ ቃል በትኩረት ተከታተልመጠበቂያ ግንብ—2000 | ሚያዝያ 1
-
-
7. ጴጥሮስ ስለ ኢየሱስ ተአምራዊ መለወጥ የነበረው ትዝታ ሕያው እንደነበር እንዴት እናውቃለን?
7 የኢየሱስ ተአምራዊ ለውጥ በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ ግንባር ቀደም የሥራ ድርሻ የሚኖራቸውን የሦስቱ ሐዋርያት እምነት ለማጠንከር ረድቷል። ያበራው የኢየሱስ ፊት፣ ነጭ ሆኖ ያንጸባረቀው ልብሱና ኢየሱስ ተወዳጅ ልጁ እንደሆነና እርሱንም መስማት እንዳለባቸው ሲናገር የተሰማው የአምላክ ድምፅ የታቀደላቸውን ዓላማ በተሳካ ሁኔታ አከናውነዋል። ይሁን እንጂ ሐዋርያቱ ኢየሱስ እስኪነሣ ድረስ ስለዚህ ራእይ ለማንም መናገር አልነበረባቸውም። ይህ ራእይ ከ32 ዓመታት በኋላ እንኳን በጴጥሮስ አእምሮ ውስጥ ገና ትናንት እንደተፈጸመ ነገር ሕያው ሆኖ ተስሎ ነበር። ጴጥሮስ ስለ ራእዩና ራእዩ ስላለው ትርጉም በመግለጽ እንዲህ ሲል ጽፏል:- “የእርሱን ግርማ አይተን እንጂ በብልሃት የተፈጠረውን ተረት ሳንከተል የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃይልና መምጣት አስታወቅናችሁ። ከገናናው ክብር:- በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና፤ እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይህን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን።”—2 ጴጥሮስ 1:16-18
-