-
ስለ አንተ የሚያስብ እረኛመጠበቂያ ግንብ—2008 | የካቲት 1
-
-
ኢየሱስ፣ ለበጎቹ የሚያስብ እረኛን ሕይወት እንደ ምሳሌ በመውሰድ እንዲህ ብሏል:- “አንድ ሰው መቶ በጎች ቢኖሩትና ከእነርሱም አንዱ ቢጠፋበት ዘጠና ዘጠኙን በተራራ ላይ ትቶ የጠፋውን ለመፈለግ አይሄድምን? እውነት እላችኋለሁ፣ የጠፋውን በግ ሲያገኝ፣ ካልጠፉት ከዘጠና ዘጠኙ ይልቅ በዚያ በተገኘው ደስ ይለዋል። እንደዚሁም ከእነዚህ ከታናናሾቹ መካከል አንዱ እንኳ እንዲጠፋ በሰማያት ያለው አባታችሁ ፈቃድ አይደለም።” (ማቴዎስ 18:12-14) ይሖዋ፣ እሱን ለሚያመልኩ ሰዎች በግለሰብ ደረጃ እንደሚያስብ ኢየሱስ እንዴት እንደገለጸ እስቲ እንመልከት።
-
-
ስለ አንተ የሚያስብ እረኛመጠበቂያ ግንብ—2008 | የካቲት 1
-
-
ኢየሱስ ምሳሌውን ሲያብራራ፣ አምላክ “ከእነዚህ ከታናናሾቹ መካከል አንዱ እንኳ እንዲጠፋ” እንደማይፈልግ ተናግሯል። ቀደም ሲል ኢየሱስ፣ ደቀ መዛሙርቱ “[በእሱ] ከሚያምኑት ከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን” እንዳያሰናክሉ አስጠንቅቋቸው ነበር። (ማቴዎስ 18:6) ታዲያ ኢየሱስ የተናገረው ምሳሌ ስለ ይሖዋ ምን ያስተምረናል? ይሖዋ፣ ‘ታናናሾቹን’ በጎች ማለትም ዓለም እምብዛም ትኩረት የማይሰጣቸውን ጨምሮ ስለ እያንዳንዱ በግ በጥልቅ የሚያስብ እረኛ ነው። አዎን፣ አምላክ እያንዳንዱን አገልጋዩን ልዩና ውድ አድርጎ ይመለከተዋል።
-