-
አለመግባባትን የምትፈቱት እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1994 | ሐምሌ 15
-
-
ከባድ አለመግባባትን መፍታት
“ወንድምህም ቢበድልህ፣ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፣ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው ባይሰማህ ግን፣ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፣ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፣ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፣ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ።—ማቴዎስ 18:15–17
አንድ አይሁዳዊ (ወይም አንድ ክርስቲያን) ከአንድ መሰል የይሖዋ አምላኪ ጋር የሚያጋጩ ከባድ ችግሮች ቢያጋጥሙትስ? በደል እንደተፈጸመበት የተሰማው ሰው የመጀመሪያውን እርምጃ ይወስዳል። ከበደለው ሰው ጋር በግል ሁኔታዎቹን አንሥቶ ይወያያል። ደጋፊዎችን ለመሰብሰብ ባለመሞከሩ ከወንድሙ ጋር ዕርቅ መመሥረት እንደሚችል አያጠራጥርም። በተለይም የነበረው ችግር ነገሮችን በትክክል ካለመረዳት የመጣ ከሆነ ችግሩ ወዲያውኑ ሊቃለል ይችላል። ስለጉዳዩ የሚያውቁት በቀጥታ በነገሩ ውስጥ ያሉበት ሰዎች ብቻ ከሆኑ ሁሉም ነገር ይበልጥ በቀላሉ ሊፈታ ይችላል።
-
-
አለመግባባትን የምትፈቱት እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1994 | ሐምሌ 15
-
-
ንስሐ የማይገባ ኃጢአተኛ ሊወገድ የሚችል መሆኑ ማቴዎስ 18:15–17 ቀላል ስለሆነ አለመግባባት እንደማይናገር ያሳያል። ኢየሱስ ከባድ በደሎችን ማመልከቱ ነበር፤ ሆኖም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁለቱ ግለሰቦች ብቻ ሊፈቱት የሚችሉት ዓይነት ነው። ለምሳሌ ያህል በደሉ የተበደለውን ሰው ስም የሚያጠፋ ሐሜት ሊሆን ይችላል። ወይም ደግሞ ቀጥሎ ያሉት ጥቅሶች ኢየሱስ ከፍተኛ ዕዳ ስለተሰረዘለት ጨካኝ ባሪያ ምሳሌ መናገሩን ስለሚገልጹ ጉዳዩ ገንዘብ ነክ ነገሮችን የሚመለከት ይሆናል። (ማቴዎስ 18:23–35) በተባለው ጊዜ ያልተከፈለ ብድር በሁለቱ ግለሰቦች መካከል በቀላሉ ሊፈታ የሚችል ጊዜያዊ ችግር ብቻ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን የተበደረው ሰው ዕዳውን አልከፍልም ብሎ ድርቅ ካለ ከባድ ኃጢአት ይኸውም ሌብነት ይሆናል።
-