-
አለመግባባትን የምትፈቱት እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1994 | ሐምሌ 15
-
-
“ወንድምህም ቢበድልህ፣ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፣ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው ባይሰማህ ግን፣ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፣ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፣ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፣ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ።—ማቴዎስ 18:15–17
-
-
አለመግባባትን የምትፈቱት እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1994 | ሐምሌ 15
-
-
ይሁን እንጂ የመጀመሪያው እርምጃ በቂ ላይሆን ይችላል። ኢየሱስ እንዲህ ዓይነቱ ሁኔታ ሲያጋጥም ምን ማድረግ እንደሚያስፈልግ ሲናገር “አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ” ብሏል። እነዚህ ሰዎች የዓይን ምሥክሮች ሊሆኑ ይችላሉ። ምናልባት ከግለሰቦቹ መካከል አንዱ የሌላኛውን ስም ሲያጠፋ ሰምተው ይሆናል፤ ወይም እነዚህ ሰዎች በአሁኑ ጊዜ በሁለቱ ሰዎች መካከል አለመግባባትን የፈጠረው ነገር ቀደም ሲል ስምምነት ተደርጎበት በጽሑፍ ሲሰፍር ተመልክተው ሊሆን ይችላል። በሌላ በኩል እነዚህ ጉዳዩን እንዲመለከቱ የሚደረጉት ሰዎች ለችግሩ መንስኤ የሆነ ማንኛውም ነገር በሚመረመርበት ጊዜ ለሚነገሩት ነገሮች ወይም በጽሑፍ ለሚሰፍሩት ቃሎች ምሥክሮች ይሆናሉ። በዚህም ወቅት ቢሆን ስለጉዳዩ ማወቅ የሚኖርባቸው በተቻለ መጠን በጣም ጥቂት ሰዎች ይኸውም “አንድ ወይም ሁለት” ሰዎች ብቻ ናቸው። ይህም ጉዳዩ ካለመግባባት የመነጨ ከሆነ ሁኔታዎች እየከረሩ እንዳይመጡ ይከላከላል።
የተበደለው ሰው ምን ዓላማ ይዞ መነሣት ይገባዋል? መሰል ክርስቲያን ባልንጀራውን ለማዋረድ መሞከር ይኖርበታልን? ክርስቲያን ባልንጀራው ራሱን እንዲያቃልል ይፈልጋልን? ኢየሱስ በሰጠው ምክር መሠረት ክርስቲያኖች ወንድሞቻቸውን ለመኮነን ችኩሎች መሆን የለባቸውም። በደል የፈጸመው ሰው ስህተቱን ካመነ፣ ይቅርታ ከጠየቀና ችግሮቹን ለማስተካከል ከጣረ በደል የተፈጸመበት ሰው ‘ወንድሙን ገንዘቡ አድርጎታል።’—ማቴዎስ 18:15
-
-
አለመግባባትን የምትፈቱት እንዴት ነው?መጠበቂያ ግንብ—1994 | ሐምሌ 15
-
-
ንስሐ የማይገባ ኃጢአተኛ ሊወገድ የሚችል መሆኑ ማቴዎስ 18:15–17 ቀላል ስለሆነ አለመግባባት እንደማይናገር ያሳያል። ኢየሱስ ከባድ በደሎችን ማመልከቱ ነበር፤ ሆኖም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ሁለቱ ግለሰቦች ብቻ ሊፈቱት የሚችሉት ዓይነት ነው። ለምሳሌ ያህል በደሉ የተበደለውን ሰው ስም የሚያጠፋ ሐሜት ሊሆን ይችላል። ወይም ደግሞ ቀጥሎ ያሉት ጥቅሶች ኢየሱስ ከፍተኛ ዕዳ ስለተሰረዘለት ጨካኝ ባሪያ ምሳሌ መናገሩን ስለሚገልጹ ጉዳዩ ገንዘብ ነክ ነገሮችን የሚመለከት ይሆናል። (ማቴዎስ 18:23–35) በተባለው ጊዜ ያልተከፈለ ብድር በሁለቱ ግለሰቦች መካከል በቀላሉ ሊፈታ የሚችል ጊዜያዊ ችግር ብቻ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን የተበደረው ሰው ዕዳውን አልከፍልም ብሎ ድርቅ ካለ ከባድ ኃጢአት ይኸውም ሌብነት ይሆናል።
-