-
የወይኑ እርሻ ሠራተኞች ምሳሌኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
“መንግሥተ ሰማያት በወይን እርሻው ላይ የሚሠሩ ሠራተኞችን ለመቅጠር ማልዶ ከወጣ የእርሻ ባለቤት ጋር ይመሳሰላል። በቀን አንድ ዲናር ሊከፍላቸው ከተዋዋለ በኋላ ሠራተኞቹን ወደ ወይን እርሻው ላካቸው። በሦስት ሰዓት ገደማም ወጥቶ በገበያ ቦታ ሥራ ፈተው የቆሙ ሌሎች ሰዎች አየ፤ እነዚህንም ሰዎች ‘እናንተም ወደ ወይኑ እርሻ ሂዱ፤ ተገቢውንም ክፍያ እከፍላችኋለሁ’ አላቸው። እነሱም ሄዱ። ዳግመኛም በስድስት ሰዓትና በዘጠኝ ሰዓት ገደማ ወጥቶ እንዲሁ አደረገ። በመጨረሻም በ11 ሰዓት ገደማ ወጥቶ ቆመው የነበሩ ሌሎች ሰዎች አገኘና ‘ቀኑን ሙሉ ሥራ ፈታችሁ እዚህ የቆማችሁት ለምንድን ነው?’ አላቸው። እነሱም ‘የሚቀጥረን ሰው ስላጣን ነው’ ሲሉ መለሱለት። እሱም ‘እናንተም ወደ ወይኑ እርሻ ሄዳችሁ ሥሩ’ አላቸው።”—ማቴዎስ 20:1-7
-
-
የወይኑ እርሻ ሠራተኞች ምሳሌኢየሱስ—መንገድ፣ እውነት፣ ሕይወት
-
-
በዚህ ቡድን ውስጥ የተካተቱ ካህናትና ሌሎች ሰዎች፣ ተራውን ሕዝብ በአምላክ የወይን እርሻ ላይ የተወሰነ ሰዓት ብቻ እንደሚሠራ ይኸውም አምላክን ከእነሱ ባነሰ መንገድ እንደሚያገለግል አድርገው ይመለከቱታል። ተራው ሕዝብ፣ በኢየሱስ ምሳሌ ላይ “በሦስት ሰዓት ገደማ” እንዲሁም በቀኑ ውስጥ በኋላ ላይ ይኸውም በስድስት፣ በዘጠኝና በመጨረሻም በአሥራ አንድ ሰዓት ከተቀጠሩት ሠራተኞች ጋር ይመሳሰላል።
የኢየሱስ ተከታይ የሆኑት ወንዶችና ሴቶች የሚታዩት ‘እንደተረገመ ሕዝብ’ ተደርገው ነው። (ዮሐንስ 7:49) አብዛኛውን የሕይወት ዘመናቸውን ያሳለፉት በዓሣ አጥማጅነት ወይም በሌላ የጉልበት ሥራ ነው። ከዚያም በ29 ዓ.ም. “የወይኑ እርሻ ባለቤት” እነዚህን ትሑት ሰዎች፣ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ሆነው ለአምላክ እንዲሠሩ እንዲጠራቸው ኢየሱስን ላከው። ኢየሱስ የጠቀሳቸው “ኋለኞች” ይኸውም በ11ኛው ሰዓት የመጡት የወይኑ እርሻ ሠራተኞች እነሱ ናቸው።
-