-
የአምላክን ፈቃድ እያደረግህ ነውን?መጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 1
-
-
“ነገር ግን ምን ይመስላችኋል? አንድ ሰው ሁለት ልጆች ነበሩት፤ ወደ አንደኛው ቀርቦ፦ ልጄ ሆይ፣ ዛሬ ሂድና በወይኔ አትክልት ሥራ አለው። እርሱም መልሶ፦ አልወድም አለ፤ ኋላ ግን ተጸጸተና ሄደ። ወደ ሁለተኛውም ቀርቦ እንዲሁ አለው እርሱም መልሶ፦ እሺ ጌታዬ አለ፤ ነገር ግን አልሄደም። ከሁለቱ የአባቱን ፈቃድ ያደረገ ማን ነው?”—ማቴዎስ 21:28–31
መልሱ ግልጽ ነው። ኢየሱስን ያዳምጡ እንደ ነበሩት ሰዎች “ፊተኛው” ብለን እንመልሳለን። ይሁን እንጂ ኢየሱስ ግልጽ ከሆነው የምሳሌው ትርጉም በስተጀርባ ሊያስገነዝበን የፈለገው በጣም አስፈላጊ የሆነው ነገር የአባቱን ፈቃድ ማድረግ መሆኑን ነው። ሁለተኛው ልጅ ለመሄድ አልፈልግም ቢልም በኋላ ግን ሄዶ ስለ ሠራ ተመስግኗል። ትክክለኛውን ዓይነት ሥራ መሥራትም የዚያኑ ያህል አስፈላጊ ነው። ሁለተኛው ልጅ በአባቱ የወይን አትክልት ቦታ ሠራ እንጂ ወደ ራሱ የወይን አትክልት ሄዶ አልሠራም።
-
-
የአምላክን ፈቃድ እያደረግህ ነውን?መጠበቂያ ግንብ—1994 | መጋቢት 1
-
-
በዛሬው ጊዜ የአምላክን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው? የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታዮች ነን ከሚሉት ወደ 2 ቢልዮን የሚቆጠሩ ሰዎች መካከል በኢየሱስ ምሳሌ ውስጥ የአባቱን ፈቃድ እንዳደረገው ታናሽ ልጅ ያደረጉት ስንቶቹ ናቸው? መልሱን ማግኘት አያስቸግርም። እውነተኛ የኢየሱስ ክርስቶስ ፈለግ ተከታዮች ይሠሩታል ብሎ የተናገረለትን ሥራ የሚሠሩ፣ ማለትም “አስቀድሞም ወንጌል ለአሕዛብ ሁሉ ይሰበክ ዘንድ ይገባል” የሚለውን ትእዛዙን የሚፈጽሙ መሆን አለባቸው። (ማርቆስ 13:10) በዓለም ዙሪያ ከአራት ሚልዮን ተኩል የሚበልጥ ቁጥር ያላቸው የይሖዋ ምስክሮች ሰላምና አስተማማኝ ኑሮ የሚመጣው የሰው ልጆች ብቸኛ ተስፋ በሆነችው መንግሥት አማካኝነት እንደሆነ በማመልከት የአምላክን መንግሥት ምሥራች በትጋት በመስበክና በማስተማር ላይ ይገኛሉ። የአምላክን ፈቃድ በማድረጉ ረገድ ሙሉ ተሳትፎ አለህን? ኢየሱስ እንዳደረገው የመንግሥቱን ምሥራች ትሰብካለህን?—ሥራ 10:42፤ ዕብራውያን 10:7
-